ከ«የኡር-ናሙ ሕግጋት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 22፦
:7. የሰው ሚስት ሌላውን ሰው በማዳራት ብትወስድ፣ ሴቲቱ ትገደል፣ ወንዱ ግን ነጻ ነው።
:8. አንድ ሰው የሌላውን ገረድ በግፍ ቢወስድ፣ ሰውዬው 5 ሰቅል (ብር) ይክፈል።
:9. አንድ ሰው የመጀመርያ ግዜ ሚስት ቢፈታ፣ አንድ ሚናምናን ('ምናን'፤ 60 ሰቅል) ይክፈላት።
:10. አንድ ሰው ጋለሞታን ቢፈታ፣ ግማሽ ሚናምናን (30 ሰቅል) ይክፈላት።
:11. አንድ ሰው ያለ ትዳር ውል ጋላሞታን ቢወስድ፣ ብር መክፈል የለበትም።
:13. አንድ ሰው ጠንቋይ ነው ተብሎ ቢከሰስ፣ በወንዝ ውስጥ በመግባት ይፈረድ፤ የዋሕነቱ ከተረዳ ከሳሹ 3 ሰቅል ብር ይክፈለው።
:14. አንድ ሰው የሌላውን ሚስት አመንዝራ ናት ብሎ ቢከስሳት፤ በወንዝ ውስጥ ገብታ የዋሕነቷ ከተረዳ ከሳሿ የሚናየምናን ሢሦ (20 ሰቅል) ይክፈላት።
:15. የዕጩ አማች ወደ ዕጩ-አማቱ ቤት ገብቶ፣ አማቱ ግን ከዚያ ሴት ልጁን ወደ ሌላ አማች ቢሰጣት፣ አማቱ ለተጣለው ዕጩ 2 ዕጥፍ ጥሎሽ ይመልሰው።
:17. አንድ ባርያ ከከተማው ውጭ ቢያመልጥ፣ ከዚያም አንድ ሰው ቢመልሰው፣ ጌታው ለመለሠው ሰው 2 ሰቅል ይክፈለው።
:18. አንድ ሰው የሌላውን ዓይን ቢያጠፋ፣ ግማሽ ሚናምናን ይክፈለው።
:19. አንድ ሰው የሌላውን እግር ቢቆርጥ፣ 10 ሰቅል ይክፈለው።
:20. አንድ ሰው በግፍ የሌላውን አካል በዱላ ቢሰብር፣ አንድ ሚናምናን ይክፈለው።
:21. አንድ ሰው የሌላውን አፍንጫ በቢላዋ ቢቆርጥ፣ 2 ሢሶ ሚናምናን (40 ሰቅል) ይክፈለው።
:22. አንድ ሰው የሌላውን ጥርስ ቢሰብር፣ 2 ሰቅል ይክፈለው።
:25. አንዲት ገረድ እመቤትዋን ብትሰድብ፣ አፏን በ1 ሊትር ጨው ትታጠብ።