ከ«የኡር-ናሙ ሕግጋት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 26፦
:14. አንድ ሰው የሌላውን ሚስት አመንዝራ ናት ብሎ ቢከስሳት፤ በውንዝ ውስጥ ገብታ የዋሕነቷ ከተረዳ ከሳሿ የሚና ሢሦ (20 ብር) ይክፈላት።
:15. የዕጩ አማች ወደ ዕጩ አማቱ ቤት ገብቶ፣ አማቱ ግን ከዚያ ሴት ልጁን ወደ ሌላ አማች ቢሰጣት፣ አማቱ ለተጣለው ዕጩ 2 ዕጥፍ ጥሎሽ ይመልሰው።
:17. አንድ ባርያ ከከተማ ቢያመልጥ፣ አንድ ሰውም ቢመልሰው፣ ባሉጌታው ለመለሠው ሰው 2 ብር ይክፈለው።
:18. አንድ ሰው የሌላውን ዓይን ቢያጠፋ፣ ግማሽ ሚና ይክፈለው።
:19. አንድ ሰው የሌላውን እግር ቢቆርጥ፣ 10 ሸከል ብር ይክፈለው።