ከ«መጽሐፈ ኩፋሌ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Rescuing 1 sources and tagging 0 as dead.) #IABot (v2.0.8.8
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
 
መስመር፡ 1፦
'''መጽሐፈ ኩፋሌ''' በ[[ኢኦተቤ|ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን]] [[መጽሐፍ ቅዱስ]] ውስጥ በ[[ዲዩትሮካኖኒካል]] መጻሕፍት አንዱ ነው። በሌሎቹ አብያታ ክርስትያናት ግን ዛሬ የማይቀበል መጽሐፍ ወይም ''ሲውዴፒግራፋ'' ይባላል። ነገር ግን ለቀድሞው የቤተ ክርስቲያን አበው ታውቆ የጥቅስ ምንጭ ሆነላቸው። የመጽሐፉ ግሪክ ትርጉም የሚታወቀው ከቅዱስ [[ኤፒፋንዮስ]] ጥቅሶች ባቻ ሳይሆን እንዲሁም በ[[ዩስቲን ሰማዕት]]፣ በ[[ኦሪጄን]]፣ በ[[ዲዮዶሮስ ዘአንጥያክያ]]፣ በ[[ኢሲዶር ዘሰቪላ]]፣ በ[[አሲዶር ዘእስክንድርያ]]፣ በ[[ዩቲክዮስ (አቡነ እስክንድርያ)]]፣ በ[[ዮሐንስ ማላላስ]]፣ በ[[ጊዮርጊስ ሱንኬሎስ]]ና በ[[ቄድሬኖስ]] ጥቅሶች በከፊል ይታወቃል።
 
ሆኖም መጽሐፉ በ[[አይሁድ]] ሊቃውንቶች ወይም[[ሳንሄድሪን]] ከ[[1ኛው ክፍለ ዘመን]] ጀምሮ እንደ ቅዱሳን መጻሕፍት አልተቀበለምመታየቱ ነበር።ቆመ። የመፅሀፉ አንዳንድ ክፍል በ[[ቁምራን]] ዋሻ በ[[1939]] ዓ.ም. እስከተገኘእስከተገኘበት ድረስ፣ዕለት የመጽሐፉድረስ፣ [[ዕብራይስጥ]] ትርጉም ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ ነበር።ነበር።በኋላ ስለዚሁ ሁኔታ (የዕብራይስጥ ትርጉም በማጣት) መጽሐፉ በኋላ ዘመንዘመንም በ[[ሮማ ቤተ ክርስቲያን]] አለቆች አልተቀበለም።ተቀባይነት ሳይኖረው ቀርቷል። ሆኖም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ዘንድ እንዲሁም በ[[ቤተ እስራኤል]] አይሁዶች ዘንድ፣ መጽሐፉ በ[[ግዕዝ]] ስለ ተገኘ እስከ ዛሬ ድረስ ቅዱስ ተብሎ ተከብሯል።
 
መጽሐፉ እንደሚለው መላእክት የዓለሙን ታሪክ ከ[[ፍጥረት]] ጀምሮ እስከ [[ኦሪት ዘጸአት]] ድረስ (2,410 ዓመታት ሲቆጠሩ) ለ[[ሙሴ]] በ[[ደብረ ሲና]] ይተርካሉ። ዘመናት በ[[ኢዮቤልዩ]] ወይም በ49 ዓመታት ይከፋፈላሉ። ኢያንዳንዱ ኦዮቤልዩ 7 [[ሱባዔ]] ወይም የዓመት ሳምንት (7 አመት) ነው። ከ[[ማየ አይህ]] አስቀድሞ [[ደቂቃ ሴት]] ከእግዚአብሔር አምጸው ወደ [[ቃየን]] ልጆች እንደ ሔዱና እንደ ከለሱ ይላል። ክልስ ልጆቻቸውም ክፉ ረጃጅሞች ([[ናፊሊም]]) ሆነው በማየ አይህ ጠፉ። ከዚህ በኋላ የኖህን ልጆች አሳቱ። ጣኦት ሠሩ፣ መንግሥት አጸኑ፣ [[የኖህ ልጆች]] ምድርን ሁሉ ያካፈላሉ፣ [[የባቢሎን ግንብ]] ከወደቀ ቀጥሎ ወደ ርስቶቻቸው ተበተኑ። መላእክትም ለ[[አብርሃም]] ቅዱስ ቋንቋን አሳውቁት።