ከ«አቡነ አረጋዊ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
there was no data . i put all the history of abune aregawi from the book of the orthodox church which states there history
 
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit iOS app edit
መስመር፡ 2፦
 
 
አቡነ   አረጋዊ የተሰወሩበት፤ ቅዱስ ገብረክርሰቶስ በዓለ እረፍት ቅዱስ ሙሴ_እግዚአብሔር በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡(ታቦታቸው በቀጨኔ ደብረሰላም ያለ) በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ #_ ፊሊጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡
 
ጥቅምት 14 ፤  አቡነ አረጋዊ ( ዘሚካኤል )  ወቅዱስ  ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር
 
[[አቡነ አረጋዊ ዘደብረዳሞ|አቡነ አረጋዊ]] ( ዘሚካኤል )
 
፠ ከእንጦንስ ከመቃርስ እና ከጳኵሚስ የምንኵስና ሐረግ አራተኛ ትውልድ ናቸው፣
መስመር፡ 12፦
፠ ደቀ መዛሙርቶቻቸውም 6 ሺህ የደረሱ ናቸው፣
 
  ከቅዱስ ያሬድ ጋር እጅግ ይዋደዱ የነበሩ ፣  ዝማሬውንም ለመስማት ከጐንደር  ለመጣ ሲል በጸጋ አይተው  ደብረ ዳሞ ላይ  ደቀ መዛሙርቶቻቸውን ሰብሰበው ይጠብቁ የነበሩ ፡፤
 
፠ ታላላቅ የኢትዮጵያ ነገሥታትን  ለባረኩ ይመጠላቸው የነበረ ..
 
፠ አጼ ገብረ መስቀል በተመስጦ  የቅዱስ ያሬድን እግር በጦር በወጋው ጊዜ ታለቅ ግብዣን አድርገ የዛኔም  አቡነ አረጋዊ ቀድሰዋል፣ ቅዱስ ያሬድም ዘምሯል ፤ ታላቅ ሥርዓትንም አስጀምረዋል፡፡
 
___________________________________________
 
፠ ትውልዳቸው ሮም ሲሆን እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከአባታቸው #ይስሐቅና ከእናቸው #እድና  የተገኙ የቅዱሳን ፍሬ ናቸው ፤ ወንድሞቹም #ቴዎድሮስ እና #ገብረ አምላክ ይባላሉ፡፡
 
፠ የቀድሞው ስማቸው #ዘሚካኤል ነበር፡፡ “አረጋዊ” የተባሉት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ነው፡፡ በእድሜ ልጅ ሲሆኑ በመንፈሳዊ ሕይወታቸውና ሥራቸው አዋቂ ስለነበሩ አረጋዊ ብለዋቸዋል፡፡
 
፠ወላጆቻቸው ቅዱሳት መጻሕፍትን እያስተማሩ አሳደጉት፤ እሱም በመንፈስ ቅዱስ ኀይል እየጸናና እየበረታ ሄደ፡፡ ዕለት ዕለት ጧትና ማታም ወደቤተክርስቲያን እየሄደ ጸሎት ከመጸለይ አያቋርጥም ነበር፡፡እድሜውም ለጋብቻ ሲደርስ አባትና አናቱ ያገባ ዘንድ ሚስት አጩለት፡፡ እሱ ግን ፈጽሞ እምቢ አለ፤ ከሕፃንነቱ ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ እየተቃኘ የምንኵስና ሕይወትን ለመኖር ፈልጓልና፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የምንኵንስና ሕይወትን ለመኖር ወደ አባ ጳኵሚስ ዘንድ ሄደ፤ ወደ ገዳሙም በገባ ጊዜ አንድ መነኵሴ አገኙትና ‹‹ልጄ ሆይ ከወዴት መጥተሃል እነሆ አንተ ሕፃን እንደሆንክ እመለከታለሁና›› አሉት፡፡ እሱም አመጣጡ ከሮም እንደሆነና ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ የሚፈልገው ነገር እንዳለ ነገራቸው፡፡ እሳቸውም ነገሩን ከሰሙ በኋላ ወደ አባ ጳኩሚስ ዘንድ ወሰዱት፡፡አባ ጳኩሚስም በአየው ጊዜ ከመንበሩ ተነስቶ  በፍፁም ፍቅር አቅፎ ሳመው የእግዚአብሔር ጸጋ በእሱ ላይ አድሯልና፡፡ ከዚያም ቀጥሎ ስለምን ጉዳይ ወደ እሱ እንደመጣ ጠየቀው፡፡ አባ ዘሚካኤልም ‹‹እንደአንተ እንደ አባቴ መነኵሴ እሆን ዘንድ መጥቻለሁ›› አለው፡፡ አባ ጳኩሚስም ‹‹ልጄ ሆይ አንተ የንጉሥ ልጅ እንደመሆንህ መጠን የመንግሥቱ ወራሽ ነህና መንኵሰህ ለመኖር እንደምን ይቻልሃል?›› ሲል መለሰለት፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን የምድር መንግሥት ኀላፊ ጠፊ እንደሆነ ያውቃልና ከዓለም ንግሥና ይልቅ ዘለዓለማዊ መንግሥትን ይወርስ ዘንድ እንደሚሻ ያመነኵሰውም ዘንድ አጥብቆ ጠየቀው፡፡ አባ ጳኩሚስም ፈተናን ፈትኖት መቋቋም የሚችል ከሆነ እንደሚያስገባው ነግሮ የተለያዩ ፈተናዎችን ፈትነው፡፡ አባ ዘሚካኤልም የተባለውን የታዘዘውን ሁሉ በትጋት ፈጸመ፡፡ አባ ጳኵሚስም ስለሃይማኖቱ ጽናት ስለጠባይና ስለቅንነቱ እጅግ አድርጐ ወደደው፡፡ ከዚያም አስኬማው ወይም ቆቡ ላይ ወደ እግዚአብሔር ጸልዮ አመነኰሰው፤ ስሙንም ዘሚካኤል ብሎ ጠራው፤ በዚህ ጊዜ #እድሜው 14 ዓመት ነበር፡፡
 
፠አባ ዘሚካኤል አስኬማ ካደረገ በኋላም በታላቅ ትጋቱ በጸሎቱና በጾሙ አባ ጳኵሚስ ተደነቀ፡፡ ስለሱም ዝናው በየሀገሩ ሁሉ እስከ አባቱ አገር ሮም ድረስ ተሰማ፡፡ አባ ዘሚካኤል ገና በሕፃንነቱ የምንኵስና ማዕረግ መቀበሉን ከሰሙ በኋላ ወደ እሱም 8 ቅዱሳን የመጡ ነበሩ፡፡ እነሱም፦ አባ #_ ሊቃኖስ ከቁስጥንጥንያ(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ )፣ አባ #_ ይምዓታ (ገዳማቸው በኃውዜን የሚገኝ (ትግራይ) ከሀገረ ቁስያ፣ አባ #_ ገሪማ ከሮም(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ ፣ ከአንፆኪያ አባ #_  ድሕማ፣ ከቂልቅያ አባ #_ ጉባ፣ ከእስያ አባ #_ አፍጼ፣ ከሮሚያ አባ #_ ጴንጠሌዎንከሮም(ገዳማቸው በአኵሱም የሚገኝ ) ፣  ከቂሳርያ አባ አሌፍ ነበሩ፡፡ እነሱም አባ ጳኵሚስ የምንኵስናውን አፅፍ አጐናፀፏቸውና አመነኮሷቸው፡፡ ለእያንዳንዳቸውም ስማቸውን ሰየሟቸው፡፡ እኒህም አባቶች ስለትዕግስት፣ አርምሞ፣ ትህትና፣ ስለሥርዐተ ማኀበር አመሠራረት ከአባ ጳኵሚስ ዘንድ ተማሩ፡፡
 
    ከዚህ በኋላ በዚያ ገዳም ለብዙ ዓመታት በፍቅር በአንድነት ከአባ ቴዎድሮስ ጋር ተቀመጡ፡፡ በዚህን ጊዜ ግን አባ ጳኩሚስ አርፈው አባ ቴዎድሮስ ተተክተው ነበር፡፡ እነዚህም አባቶች ወደየሃገራቸው ሄደው ማስተማርና ሃይማኖትንማስፋፋት እንዳለባቸው ተስማምተው ወደየሀገራቸው ተመለሡ፡፡ አባ ዘሚካኤል ግን በዚያው ቆየ፡፡ እሱ ልቡን የነካችዉ ዜናዋንም የሰማላት ሃገር ነበረችና፡፡ ይህቺውም ሃገራችን #ኢትዮጵያ ነበረች፡፡ እሱም ማንም ሰው ሳያውቅና ሳያየው ከሁለቱ ደቀመዛሙርቱ ጋር ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው መጥተው ጐብኝተዋታል፡፡ ያለመምህራንና ያለአስተማሪ ያመነች የዚህችን ሀገረ እምነቷንና ሥነስርዐቷን ተመልክቶ ተደነቀ፡፡ እነዚያን 8 መነኰሳትም ከያሉበት ስለሃገሪቷ እየነገረ ጠራቸው የሚገርመው ግን እነሱም ስለዚህች ሀገር እንደሰሙ ያለምንም ማመንታት መጥተዋል፡፡ እነሱም ሕዝቡን እንደሰሙት አገኙት፡፡ አባ ዘሚካኤል አቡነ አረጋዊ የሚለውን ስያሜ ያገኙት ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ትህትናቸውና ታዛዥነታቸው እሳቸውሲመነኩሱ ገና ሕፃን ነበሩ ስራቸው ግን የአረጋውያን ነበርና አንተስ ሐፃን አይደለህም የልጅ አዋቂ ነህ ሲሉ #አረጋዊ አሏቸው፡፡ አባታችን አቡነ አረጋዊ ወደ ኢትዮጵያ የገቡበትም ቀን ጥቅምት 11  ነበር ፡፡
 
አቡነ አረጋዊ በኢትዮጵያ ሲኖሩ በሄዱበት ስፍራ ብቻቸውን የሚፀልዩበትን ቦታ ሁል ጊዜ ይፈልጉ ነበር፡፡ አንድ ቀንም በመንገድ እየሄዱ ሳሉ ትልቅ ተራራን (ደብረ ዳሞን) ተመለከቱ፤ ከሦስተኛው ቀን በኃላም የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ‹‹አንተ እግዚአብሔር ያከበረህ ቅዱስ ሆይ ምን ያስጨንቀሃል›› አለው፡፡ አባታችንም አቡነ አረጋዊም ‹‹ከዚህች ተራራ ላይ ወጥቼ ስለኃጥያቴ እናዘዝና እለማመን ስለበደሌም ይቅርታን እጠይቅ ዘንድ እወዳለሁ›› አለው፡፡  ቅዱስ ሚካኤልም እንዲፀልይና ታላቅ ዘንዶም ወደርሱ እንደሚላክለት ነገረው፡፡ በሦስት ሰዓትም ዘንዶው መጣ፤ አባታችንም የዘንዶውን ጅራት ይዘው ወደ ላይ ወጡ ብቻቸውን አልነበሩም ፡፡ ዘንዶው እንዳያስደነግጣቸውና እንዳይጐዳቸው ሰይፍን ይዞ ቅዱስ ሚካኤል ይጠብቃቸው ነበር እንጂ፡፡ ቢዚያችም ሰዓት ተራራዋ ደብረ ታቦርን መስላ ነበር:: በዚህችም ላይ ንጉሥ አጼ ገብረ መስቀል ቤ/ክ ከአነጹ በኃላ  የቅዳሴ ቤቱ ዕለት አቡነ አረጋዊ ቀድስው ንጉሡም ሠራዊትም ሕዝቡም ጳጳሳቱም  ጭምር ሥጋ ወደሙን ተቀብለዋል፡፡ ንጉሡም በረከተን ከአባታችን ተቀብሉ ወደ አኵሱም ተመልሷል፡፡ ሲመለስም ሰርቶት የነበረውን ድልድላይ ላፍረሰው ወይ ሲላቸው ዳሕምሞ ብለውታል ትርጕሙም  ‹‹የሰራኸውን ደረጃ ናደው ፥ አፍርሰው እንጂ አትተወው›› ፡፡ ከዚ በመነሳት ዳሞ ተብላለች፡፡
 
እግዚአብሔርም ሰማያዊ ኅብስት ትሁነህ ብሎ ደብረ ዳሞን ስጥቶዋቸዋል ይህም በመንፈስ ለሚወለዱት ልጆቹ እስከ ዘለዓለም ማርፍያ እንድትሆን ነው ፡፡
 
 
  አባታችን አቡነ አረጋዊም የእርጅና ዘመናቸው በደረሠ ጊዜ እግዚአብሔር ወደ እርሱ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ ይኸውም ‹‹መታሰቢያህን ያደርግ በጸሎትህም የተማመነውን ሁሉ እኔ በመላእክት ፊት ሞገስን ቧለሟልነትን እሰጠዋለሁ፤  በእውነተኛ ሀይማኖት ሁሉ የገድልህን መጽሐፍ የጻፈ፤ ያጻፈ፤ የተረጐመ እኔ ስሙን በሕይወት መጽሐፍ እጽፈዋለሁ፤ ይህ ሁሉ ላደረገም እስከ 14 ትውልድ ድረስ እምርልሀለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን አልሞተም በዓመቱ "ሞትን የማይቀምሱ አሉ፡፡" ብሎ እንደተናገረው /ማቴ 16 ፥ 28/ ጥቅምት 14 ቀን 558 ዓ/ም #ተሠወረዋል፡፡ ይህም እንዲህ ነው
 
አባታችን አቡነ አረጋዊ ማትያስ ለተባለው ደቀ መዛሙር ጌታችን ተገልጦ የሰጣቸውን ቃል ኪዳንና ይህ መጽሐፍ ተጽፎ ለልጅ ልጅ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ነገሩት፤ (መዝ ፻፲፩/፻፲፪፥፮) ወንድሞቹ ደቀ መዛሙርቶቹ በተሰበስቡበትም ሁሉንም ከአስተማሩ በኋላ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ በሥጋ አታዩኝም›› አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም በመሪር ኃዘን እግራቸው ሥር ወድቀው አለቀሱ፤  አባታችን አቡነ አረጋዊም አጽኗኗቸው፡፡ ጥቅምት ፲፬ ቀን ቅዱስ አባታችን አቡነ አረጋዊ በ፺፱ (99) ዓመታቸው ተሰወሩ፤ በዚያም #ከመቋሚያና #ከመስቀል በስተቀር ምንም የተገኘ የለም፡፡ ገድላቸውንም ደቀ መዛሙርታቸው ማትያስ እና ዮሴፍ ጽፈዋል፡፡ ከዚያም አባ ማትያስ ደብረ ደሞን ለማስተዳደር ተሾመዋል፡፡
 
ከጻድቁ አባት በረከት ይክፈለን፤ በቃልኪዳናቸው ይጠብቀን፤ አሜን፡፡
መስመር፡ 43፦
<nowiki>#</nowiki>_ እግዚአብሔር አምላክህ አንተን መርጦሃልና እንደ ኹለቱ ነቢያት ለተከወነ መሠወርህ ሰላምታ የሚገባህ ደግ አገልጋይና የታመንህ መጋቤ ቤቱ ቅዱስ አረጋዊ ሆይ በዐሥሩ አህጉር ተሹመህ ኀምስቱን መካልይ የተቀበልህ አንተ አይደለህምን?፡፡ _#
 
          #መልክአ አቡነ አረጋዊ
 
፨#ቅዱስ ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር በዓለ #ዕረፍታቸው_፡፡(ታቦታቸው በቀጨኔ ደብረሰላም ያለ)
 
ታሪኩ ከሙሽራው ቅዱስ ገብረ ክርስቶስና ከቅዱስ ቶማስ ዘቶርማቅ ጋር ተመሳሳይ የሆነው(ቅዱስ ያሬድ ለእመቤታቸን ( ትዕግሥትኪ ፈድፈደ እምትዕግሥተ ኢዮብ ጻድቅ ፤ወእማርቆስ #ዘቶርማቅ ፤ ወገብረ ክርስቶስ መርዓዊ ተወካፌ ሕማም መጽዕቅ፡፡ ) ብሎ እንደጻፈው ቅዱስ ቶማስ ዘቶማርቅ እንደ ኢዮብ ታጋሽ  የሆነ ጻድቅ ነው፡፡ ይህም  የእግዚአብሔር ሰው የተባለ ትዕግሥኛው    ቅዱስ ሙሴ ዕረፍቱ ነው፡፡
 
፠፠ ፠፠፠ ፠፠፠ ፠
መስመር፡ 53፦
/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/
 
    #share
 
.Facebook...
መስመር፡ 67፦
<nowiki>http://tiktok.com/@finotehiwot</nowiki>
 
      www.finotehiwotsundayschool.com
 
<nowiki>#</nowiki>Share #like