ከ«እስራኤል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
Tags: Visual edit በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
No edit summary
Tags: Visual edit በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
መስመር፡ 30፦
የመጀመሪያ ሰዎች ከአፍሪካ ወደ እስራኤል እንደወጡ ይነገራል። በመካከለኛው የነሃስ ዘመን ከንዓናዊ እንደኖሩና የይሁዳና እስራኤል ግዛት በብረት ዘመን እንዳሉም የቅሪት ተመራማሪዎች አስረድተዋል። አዲሱ የአሱራውያን ግዛት እስራኤልን በ720 ዓዓ አጥፍቶ እስራኤል የመገነጠል አደጋ ደርሶባት ነበር። ይሁዳ የባቢሎኒያን፣ የፋርስና የግሪክ ተከታታይ ግዛቶች ገዝቶ ነበር። የመቃብያን አመፅን ተከትሎ የሃስሞንያ ግዛት በ110 ዓዓ ተመስርቷል። ይህም ግዛት ከሮማ ግዛት በ63 ዓዓ ጋር ሲዋሀድ፣ በ37 ዓዓ ደግሞም የሄሮድ ስርወ መንግስት ማቋቋም ጀመረ። ነገር ግን በ6 ዓዓ የይሁዳ ግዛት የሮማ አውራጃ አካል ሆኖ ነበር።
 
በወቅቱ የነበረውን እርስ በርስ ሽኩቻ ተከትሎ እስራኤል በ70 ዓም መፍረስ ጀመረች፣ አይሁዳውያን መበተን ሲጀምሩ ግዛታቸው ከይሁዳ ወደ የሶርያ ፍልስጤም የሚል ስያሜ ተሰጠው። በ7ተኛው ክፍል ዘመን እስራኤል በአረብ እጅ ቁጥጥር ስር ዋለች። ይህም እስከ 1099 ዓም በነበረው የመጀመሪያው መስቀል ጦርነት ድረስ ነበር። ከ13ተኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የግብፁ ማምሉክ ሱልጣኔት ሌቫንትን ሲቆጣጠር ኦቶማኖች በ1517 ዓም አሸንፈው ተቆጣጠሩ። ከዛም ግዜ ጀምሮ አምባገነናዊው የፅዮን ንቅናቄ እስራኤላውያን ማከናወን ጀመሩ። ይህም ንቅናቄ እስራኤላውያን ወደ ታሪካዊ ቦታቸው እንዲመለሱ ሳይሆን በአይሁድ የሚመራ አምባገነናዊ የአለም መንግስት መመስረት ነበረ። አንደኛውን የአለም ጦርነት ተከትሎ፣ የእንግሊዝ ግዛት የሌቫንትን አጠቃላይ ቦታ ቅኝ ገዛ።ገዛች። የተባበሩት መንግስታት በ1947 ዓም ይህንን ግዛት ከፍሊስጤም ቢያስለቅቅና፣ የእስራኤልና የአረብ ነፃ ድንበር ቢሰጥም፣ የአረብ መሪዎች ይህንን ስምምነት አልተቀበሉትም። ምንም እንኳን አጭር ጦርነት ቢያረጉም፣ እስራኤል በ1948 ዓም እንደ ነፃ ሀገር መሆን ጀመረች፣ የተወሰኑት የቀድሞ ቦታዎቿን ብታስመልስም ዌስት ባንክና ጋዛ ለግብፅና ለዮርዳኖስ ተተወ። እስራኤል ይህንን ግዛት ለማስመለስ ከአረብ ሀገራት ጋር ብዙ ግጭቶችን ብታረግም በኋላ ከግብፅና ከዮርዳኖስ ጋር ጥሩ ያለሰለሰ ግንኙነት ጀመሩ።
 
የእስራኤል "ቤዚክስ ሎው" (መሰረታዊ ህግ) የሚደነግገው አይሁዶች እስራኤልን እንደሚመሯትና ሉዐላዊ ሀገር እንደሆነች ነው።