ከ«ሚስቶች በኖህ መርከብ ላይ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
ከ[[ማየ አይህ]] በፊት በነበሩ ዕለታት ስለ ኖሩ በ[[ኖህ]] መርከብ ላይ ስለ ተገኙ ስለ አራቱ ሴቶች [[ኦሪት ዘፍጥረት]] ምንም እንኳን ዝም ቢል፣ ከሌላ ምንጭ ስለነዚሁ ሴቶችና በተለይ ስለ ስሞቻቸው የተገኘው [[አፈ ታሪክ]] በርካታ ነው።
 
በጥንታውያን እምነት ዘንድ፣ የ[[ሴም]]፣ የ[[ካም]]ና የ[[ያፌት]] ሚስቶች ዕጅግ የረዘማቸው ዕድሜ ሲኖራቸው ከመጠን ይልቅ ለብዙ መቶ ዓመታት ኑረው ለያንዳንዱ ትውልድ ትንቢት እየተናገሩ ኖሩ። እነኚህ [[ሲቡሎች]] ተብለው ለ[[ግሪኮች]] ለ[[ሮማውያን]]ም እንደ ቅዱሳን መጻሕፍት የተቆጠሩየተቆጠሩት የ[[ሲቡላውያን መጻሕፍት]] ደራሲዎች እንደ ነበሩ ታመነ። የሮማውያን ቅጂ በ[[397]] ዓ.ም. አካባቢ በእሳት ተቃጥሎ ዛሬ የሚታወቁ የ[[ሲቡላውያን ንግሮች]] የተባሉት ሰነዶች ኦሪጂናል መሆናቸው ለምሁሮች አይመስላቸውም። ከመጀመርያ ሲቡሎች በኋላ ሌሎች ሲቡሎች እንደ ተከተሉ ለንግሮቹም እንደ ጨመሩ ይታስባል።
 
በ[[መጽሐፈ ኩፋሌ]] የሴም፣ የካምና የያፌት ሚስቶች እንዲሁ ተብለው ይሰየማሉ፤
*የሴም ሚስት፣ '''ሰደቀተልባብ'''
*የካም ሚስት፣ '''አኤልታማኡክ''' (ወይም በለላበሌላ ትርጉም '''ናኤልታማኡክ''')
*የያፈትየያፌት ሚስት፣ '''አዶታነሌስ''' (ወይም በለላበሌላ ትርጉም '''አዳታነሥስ''') ናቸው።
 
ከዚህ በላይ ሦስቱ የኖህ ልጆች ከጥቂት ዓመት በኋላ ከ[[አራራት]] ሠፈር በየአቅጣጫው ሂደው ለሰው ልጆች ሁሉ እናቶቻቸው ለሆኑት ለሚስቶቻቸው ስሞች የተባሉ 3 መንደሮች እንደ መሠረቱ ይታረካል።
 
በኋላ ዘመን የክርስቲያን ጸሓፊ [[ቅዱስ አቡሊድስ]] ([[227]] ዓ.ም. የሞቱ) በ[[ሶርያ ታርጉም]] ዘንድ ለዚህ ተመሳሳይ የሆነ ታሪክ አወሩ።መዘገቡ። ነገር ግን እዚህ የሴምና የካም ሚስቶች ስሞች እንዳለዋወጡ ይመስላል። እሱ እንዲሁእንዲሁ፦ "«የኖህ ልጆች ሚስቶች ስሞች አንዲሁ ናቸው፤ የሴም ሚስት፣ '''ናሃላጥ ማህኑክ'''፤ የካምም ሚስት፣ '''ዘድካት ናቡ'''፣ የያፈትም ሚስት '''አራጥካ''' ይባላሉ"» ብሎ ጻፈ።
 
[[ጆን ጊል]] ([[1697 እ.ኤ.አ.|1697]]-[[1771 እ.ኤ.አ.]]) በመጽሓፍ ቅዱስ ነክ አስተያይቶቹ ስለ አንድ የ[[ዓረብ]] አፈ ታሪክ የጻፈው እንዲሁ ነው፤ "«የሴም ሚስት ስም '''ዛልበጥ''' ወይም '''ዛሊጥ''' ወይም '''ሳሊት''' ሲሆን፣ የካምም ድግሞደግሞ '''ናሓላጥ''' ተባለች፣ የያፌትም ደግሞ '''አረሢሢያ''' ተባለች።
 
በ'ሲቡላውያን ንግሮች' ዘንድ፣ ከሲቡሎቹ የአንዲቱ ስም ለ'''ዛልበጥ''' ተመሳሳይ ነበረች፤ነበረ፤ እሷም የ"«ባቢሎን ሲቡል"» '''ሳምበጥ''' ነበረች። ከጥፋት ውሃ 900 አመት በኋላ ወደ [[ግሪክ (አገር)|ግሪክ]] አገር ሄዳ የንግሮች ጽሑፍ እንደ ጀመረች ብላ ጻፈች። ከዚያ በላይ የጻፈችው ጽሁፍ ከማየ አይህ አስቅድመውአስቀድሞ የኖሩትየነበሩ የቤተሠቧ ስሞች ይታርካሉ።ይታርካል። እነሱም አባቷ ''ግኖስቲስ''፣ እናቷ ''ኪርኬ''፤ እህቷም ''ዒሲስ'' ናቸው። በሌሎች ጥንታዊ ምንጮች ደግሞ '''ሳባ''' የምትባል ሲቡል ኖረች።
 
በ[[ከለዳዊ]]ው [[ቤሮሱስ]] ዘንድ (ከ[[ክርስቶስ]] በፊት በ280 ዓመት ያህል የጻፈ) የልጆቹ ሚስቶች '''ፓንዶራ፣ ኖኤላ፣ ኖኤግላ''' ተብለው ተሰየሙ።
 
በ[[አይርላንድ]] አፈ ታሪክ ስለ ሦስቱ ልጆችና ስለ ሚስቶቻቸው የሚተረተው ብዙ አለ። በዚሁ ምንጭ ሚስቶቹ '''ኦላ፣ ኦሊቫ፣ ኦሊቫኒ''' ይባላሉ። እነኚህም ስሞች የተወሰዱ [[ኮዴክስ ጁኒየስ]] ከተባለው ጥንታዊ ([[700]] ዓ.ም.) [[እንግሊዝ]] [[ብራና ጥቅል]] ይመስላል። ይኸው ጽሕፈት እንደ ረጅም [[ግጥም]] ሆኖ በገጣሚው በ[[ካድሞን]] እንደተጻፈ ይታሥባል። እዚህ ደግሞ የኖህ ሚስት '''ፔርኮባ''' ትባላለች።
 
የ[[ሀንጋሪ]] አፈ ታሪክ ደግሞ ስለ ያፌትና '''ኤነሕ''' ስለ ተባለችው ስለ ሚስቱ አንዳንድ ተረት አለበት። ይህ መረጃ የሚገኘው የ[[አንጥያኮስ]] [[ጳጳስ]] [[ሲጊልበርት]] ከተጻፉት ዜና መዋዕል እንደ ሆነ ይባላል።
 
በደቡብ [[ኢራቅ]] በሚኖሩት በጥንታዊ [[ማንዳያውያን]] ሐይማኖት ተከታዮች መጻሕፍት ዘንድ፤ የኖህ ሚስት '''ኑራይታ''' ወይም '''አኑራይጣ''' ተባለች። በ11ኛ ክፍለ-ዘመን የኖረው አይሁድ ጸሐፊ [[ራሺ]] እንዳለው የኖህ ሚስት የላሜህ ሴት ልጅ '''ናዕማህ''' ነበረች። እንዲሁም ከ[[1618]] ዓ.ም. ብቻ በሚታወቀው "ያሻር መጽሐፍ" በሚባለው ጽሕፈት ዘንድ፣ አንዲሁም ባንዳንድ የ[[አይሁድ]] መምሁራን ዘንድ፣ የኖህ ሚስት ስም የቃየል ልጅ '''ናዕማህ''' ተባለች። ነገር ግንግን፤ ጥንታዊ መጽሀፈ ኩፋሌ ስምዋ '''አምዛራ''' ተብሎ ይሰጣል። "ናዕማህ" የሚለው የካም ሚስት ስም ለኖህ ሚስት ስም በአይሁድ ልማድ እንደ ተሳተ ጆን ጊል ሐሳቡን አቅርቧል።
 
በመጨረሻም፣ በ[[ዩናይትድ ስቴትስ]] በሚገኘው በ[[ሞርሞን]] ሃይማኖት ('የየሱስ ክርስቶች መጨረሻ ዘመን ቅዱሳን') መጻሕፍት ዘንድ፣ የካም ሚስት ስም '''ኢጅፕተስ''' ነበረ።
 
[[Category:መጽሐፍ ቅዱስ]]