ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 333፦
፴፫. ትክክለኛ ሰዋስው፣ የተሟሉ ቀለሞች፣ ትክክለኛ ቅርጾች እና የመሳሰሉትን በኣሌላቸው መጠቀም ለቋንቋው መዳከም ምክንያቶች እንዳይሆኑ መጠንቀቅ ኣስፈላጊዎች ናቸው። ስሕተቶች ሲደጋገሙ ሊለመዱ ይችላል። [https://www.facebook.com/getatchew.haile?hc_ref=ARRFkxIO467tAUBLSXTt7knkXxVL2anC-a6g_DTbwgxos8h3IbXzLdfI1m-Pb68lCJ8&fref=nf] ዶክተሩ ከሰዋስው ተሳሳቶች ኣንዱ ናቸው። ፴፬. ስለ ግዕዝና ዓማርኛ ፊደላት ሲጻፍ ስለ ግዕዝ ቋንቋ የሚመስሏቸው ኣሉና ይታሰብበት። ፴፭. ፊደላችን ለኣፍሪቃውያንና ሌሎችም እንዲተርፍ በወጉ መጠቀምና መንከባከብ ይጠቅማል። [https://ethiopianreporter.com/content/%E1%8B%A8%E1%8C%8D%E1%8B%95%E1%8B%9D-%E1%89%81%E1%8C%AD%E1%89%B5/] ፴፮. "ዓማርኛ" በግዕዙ "ዐ" የማይጻ'ፈው ቀለሙ ድምጹን ስለማይወክል ነው።
 
፴፯. ብዙ ስሕተቶችና ግድፈቶች የኣሉትን ጽሑፍ በዋቢነት ለመጠቀም ኣያስተማምንም። ምክንያቱም ደራሲው ኣስፈላጊዎቹን ጥንቃቄዎች ኣለማድረጉን ስለሚያሳይ ኣለመግዛት ወይም መተቸት ሳይሻል ኣይቀርም። ለምሳሌ ያህል "ነው" እና "ነህ" የመሳሰሉትን ቃላት "ነዉ" [https://welkait.com/?p=16546&fbclid=IwAR3U4bgJOYyaxyC3LmEZRhMRvVocGHt3_y9xe65Gunl7_ADgkt9pH8aQYQA] እና "ነክ" የሚሉ ኣሉ። "ኢትዮጵያ"ን በትክክል መጻፍ የማይችሉ ፊደል በሚገባ ኣልቈጠሩም ወይም ረስተዋል ማለት ኣይደለምን? ፴፰. የኣንድኣንዶቹ ስሕተቶች ምንጮች ማተሚያ ቤቶች ናቸው። ለምሳሌ ያህል ቀደም የኣሉ ጽሑፎች ውስጥ የ"ፏ" ፊደል መስመሩ የኣለው ከላይ ሆኖ ሳለ የኣዳዲሶቹ ከታች ነው። ቀደም የኣለውን ምልክት ዶክተሩ ሲጠቀሙ የተሳሳቱ የሚመስሏቸው ኣሉ። ይኸንኑ መቀጠያ ከግዕዝ ወግ ውጪ "ፍ" ላይ ተደርጎ በቅርቡ የቀረበ ፊደልም ኣለ። ማተሚያ ቤቶች በትክክለኛዎቹ ቀለሞች ከመቶ ዓመታት በላይ የተጠቀሙ ስለሆኑ መሪዎች እንጂ ተከታይ መሆን የለባቸውም። ፴፰. ዓማርኛ ማጥበቂያ ኣይጠቀምም የሚሉ ፈረንጆችም ኣሉ። በዓማርኛ ፊደል ሲደረብ እንደእንግሊዝኛው ኣይጠብቅም። [https://en.wikipedia.org/wiki/Amharic] ፴፱. ኣንዳንድ የዓማርኛ ተጠቃሚዎች ዓማርኛ ሞክሼዎ ድምጾች የሉትም የሚሉ ኣሉ። "ኣባይ"ና "ዓባይ" ኣንድ ኣለመሆናቸው ለመሣሣታቸው ምስክሮች ናቸው። ፵. ዶክተሩ ለመንግሥት የኣቀረቡት የፓተንት ማመልከቻ በወጉ ጥበቃ ሳይደረግለት መንግሥትና ኣብዛኛው ሕዝብ ከዶክተሩ በተሰረቁ የግዕዝ ቴክኖሎጂ ሲጠቀም ቆይቷል። ኣሁን ለውጥ መጥቷል ስለተባለ ሁሉም ሌቦች መስረቅ ማቆም ይገባቸዋል። ሌብነት ተለምዶ የዶክተሩን ሥራዎች የሚደብቁም ኣሉ። ፵፩. ይህ ጽሑፍ ብዙ ዓይነት ግድፈቶች ኣሉት፦ ለምሳሌ ያህል ኣራት ነጥብ የለውም፣ በሳድሱ “ው” ምትክ ካዕቡን “ዉ” ተጠቅሟል፣ ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ፣ ኢትዪጵያ እና ኢትዩጵያ በማለት ኣቅርቧል። [http://aigaforum.com/articles/qatar-and-ethiopia-on-somalia.pdf]
 
===ሞክሼ ኆኄያት===