ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
No edit summary |
||
መስመር፡ 9፦
እየኣንድኣንዱም በሁለት መርገጫዎች እንዲከተብ በመፍጠር ግዕዝ ከማተሚያ ቤቶች ወደ ኮምፕዩተር እንዲገባ ኣደረጉ። [[ሞዴት]] (ModEth) በመባል የታወቀውን የቃላት ማተሚያ የ[[ማይክሮሶፍት]]ን ዶስ በመጠቀም በ፲፱፻፹ ዓ.ም. [[ኣሜሪካ]] ውስጥ ለገበያ ኣቀረቡ። ጊዜውም ኮምፕዩተሮችና ማተሚያዎች በቂ ኃይል ማግኘት የጀመሩበት ነበር። ግዕዝ በኮምፕዩተር እንዲከተብ የፈጠሩበትን ዘዴ በ[[ዩናይትድ እስቴትስ]] ፓተንት መጠበቅ እንዲችሉ ቢያመለክቱም በእዚያን ጊዜ ኢትዮጵያ የፓተንት ሕግ ስለኣልነበራት [[የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል (ኢትዮጵያ)]] ሕጉ ሲወጣ ጉዳዩ ይታያል በማለት ስለወሰነ [http://archive.is/No43M] ፓተንት ኣልወጣለትም ነበር።
ግዕዝ ድምጻዊ ፊደል ስለሆነ እየኣንድኣንዱን “ሀሁሂ” ቀለም በ“ABC” ምትክ [http://en.wikipedia.org/wiki/Printing_press] እየደረደሩ ማተም ከ፲፱፻ ዓ.ም. ገደማ ጀምሮ ኢትዮጵያ ውስጥ የኣሉ ማተሚያ ቤቶች ሊጠቀሙበት ችለዋል። [https://www.facebook.com/Tenthandfourth?fref=nf] [http://ethiopianthisweek.com/the-eucalyptus-tree-and-ethiopias-first-modern-schools-and-hospitals/] በቀለሞቹ ብዛት የተነሳ ግን የእንግሊዝኛውን የጽሕፈት መሣሪያ ለዓማርኛ እንኳን መጠቀም ኣልተቻለም። ከ[[ዳግማዊ ምኒልክ]] ጀምሮ [http://www.linkethiopia.org/guide-to-ethiopia/the-pankhurst-history-library/why-cant-we-have-an-amharic-typewriter-menelik/] ብዙ ኢትዮጵያውያን ሊቆች፣ ሚኒስትሮችና ደራስያን የእንግሊዝኛውን የታይፕ መጻፊያ ለዓማርኛ መክተቢያ እንዲያገለግል ወደ ሰማንያ ዓመታት ግድም ሲመራመሩ ቆይተው ባይሳካላቸውም [http://www.quatero.net/pdf/amharic_fidelat2.pdf] ዶ/ር ኣበራ ጥረቶቻቸውን በኮምፕዩተር ኣሳክተዋል። ስለ ዓማርኛ የጽሕፈት መኪና ምርምሩም የዋቢው ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት ኣባ [[ተክለ ማርያም ሰምሃራይ]]፣ ክቡር ዶ/ር [[ሀዲስ ዓለማየሁ|ሃዲስ ኣለማየሁ]]፣ ኣቶ [[ዓለሙ ኃብተ ሚካኤል]]፣ ኢንጂነር [[ኣያና ብሩ]]፣ ዶ/ር ዓለመ ወርቅ፣ ኣለቃ [[ኪዳነ ወልድ ክፍሌ]]፣ ክቡር ኣቶ [[ኣበበ ኣረጋይ]]፣ ክቡር ራስ [[ዕምሩ ኃይለ ሥላሴ]]፣ ዶ/ር ሉባክ፣ ኣቶ [[ዘውዴ ገብረ መድኅን]]፣ ብላታ [[መርስዔ ሃዘን ወልደ ቂርቆስ]]፣ ፀሓፊ ትዕዛዝ [[ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ]]፣ ክቡር ኣቶ [[ሚሊዮን ነቅንቅ]]፣ ኣቶ [[ስይፉ ፈለቀ]]፣ ክቡር ዶ/ር [[ከበደ ሚካኤል]]፣ ኣቶ [[ሳሙኤል ተረፈ]]፣ ሌላ እነ ኮሎኔል [[ታምራት ይገዙ]]፣ [[መንግሥቱ ለማ|መንግስቱ ለማ]]፣ ኣቶ [[ብርሃኑ ድንቄ]]፣ [[ብላታ ዘውዴ በላይነህ]]፣ የኔታ [[ኣስረስ የኔሰው]]፣ [[ተክለማርያም ኃይሌ]]፣ ሼክ [[በክሪ ሳጳሎ]] እና ዶ/ር [[ፍቅሬ ዮሴፍ]]ንም [http://www.dejeselam.org/2009/02/sole-african-alphabet.html] ያጠቃልላል። [http://web.archive.org/web/20130502215942/http://www.quatero.net/pdf/amharic_fidelat2.pdf] ይህ ድካማቸው በመጨረሻ ሊሳካ የቻለው ግን ዶክተሩ ምንም ቀለም ሳይቀንሱ ወይም መልካቸውን ሳይቀይሩ የጥንቱንና ትክክለኛ የግዕዝ ቀለሞች [http://www.bbc.co.uk/nature/humanplanetexplorer/africa/ethiopia] በኮምፕዩተር እንዲቀርቡ ስለኣደረጉ ነው። [http://www.linkethiopia.org/guide-to-ethiopia/the-pankhurst-history-library/printing-developments-in-the-1920s-and-increased-study-abroad/] [http://www.worldscriptures.org/pages/ethiopic.html] የእነዚህ ምሁራን በታይፕ መሣሪያ ሙከራዎች የመጠቀም ዓላማዎች ባይሳኩላቸውም ዶክተሩ በእዚያው የፊደል ገበታ ምኞታቸውን ኣሳክተውላቸዋል። [http://archive.fo/uKbLy] በተጨማሪም የ[[ቢለን]]፣ [[ጉራጌ]] እና [[ሳሆ]] ምሁራን የቋንቋ ፊደሎቻቸውን እንዲጨምሩላቸው ናሙና ጽሑፎችን ልከውላቸዋል። ከእዚሁ ጋር በማያያዝ እየኣንድኣንዱ ቀለም በሁለት መርገጫዎች እንዲከተብ ኣዲስ የኣከታተብ ዘዴ ፈጥረው ኣዳዲስ የፊደል
የግዕዝን [[ቀለም]] (Glyph) በኮምፕዩተር በቀላሉና በቀልጣፋ ዘዴ ማቅረብ ስለቻሉ ሕዝቡ ከማተሚያ ቤቶች በተሻለ ሁኔታ በፊደሉ መሥራት ችሏል። በእዚህም የተነሳ ሕዝቡ መጽሓፍትንና የመሳሰሉትን ለማሳተም በየማተሚያ ቤቶች ወረፋ ከመጠበቅና ከመንግሥት እገዳ ተርፎ የእራሱ ኣታሚ ሆኗል። [http://www.fettan.com] [https://www.facebook.com/Tenthandfourth?fref=nf] ዘዴውም በዓማርኛ ሳይወሰን ለሁሉም የግዕዝ ቀለሞች መክተቢያና ማተሚያ ከሌሎች የዓለም ፊደላት እኩልና ጎን በሚገባ ሥራ ላይ እየዋለ ነው። [http://www.slideshare.net/nebiyu1/ethiopia-historic-highlights-july-21-2013] ይህ የዓማርኛ ውክፔዲያ ገጽ እንደ ሌሎች ትክክለኛ የዓለም ባለ ፊደል ቋንቋዎች ገጾች የቀረበውም በእዚሁ በግዕዝ የ[[ዩኒኮድ]] መደብ ቀለሞች ነው። [https://meta.wikimedia.org/wiki/There_is_also_a_Wikipedia_in_your_language] ሌላው የ[[ትግርኛ]] ውክፔዲያ ገጽ ነው። የዶ/ር ኣበራ ግኝቶች [http://www.google.com/patents/US20090179778] (Ethiopic Character Entry - July 16, 2009 ሕትመት) በግዕዝ ሳይወሰኑ ለኣንድኣንድ የዓለም ፊደሎች ኣዳዲስ ኣጠቃቀሞችና ግኝቶች ስለጠቀመ ስምንት የዩናይትድ እስቴትስ ፓተንቶች ውስጥና ሦስት የፓተንት ማመልከቻዎች ውስጥ (Citing Patents) ተጠቅሷል። [http://scholar.google.com/scholar?rlz=1T4GUEA_enUS611US611&um=1&ie=UTF-8&lr=&cites=16591930435158160807] [http://www.google.com/patents/US20090179778#forward-citations] [https://www.quora.com/What-are-some-arguments-against-claims-that-sub-Saharan-Africans-are-intellectually-inferior] ቊጥሮቻቸውም [https://www.google.com/patents/US8381119]፣ 8645825፣ 8700653፣ 8706750፣ 8762356፣ 8812733፣ 9715111፣ 9723061፣ 9733724፣ 20110173558፣ 20160042059 እና 2963525A1 ናቸው። [https://www.google.com/patents/US20090179778#backward-citations] እነዚህ ኢትዮጵያን የሚያኮሩ ሥራዎችም ናቸው።
|