ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 68፦
[https://groups.yahoo.com/neo/groups/rastareasonings/conversations/messages/890]
[http://www.ethiopianstories.com/component/content/article/55-science-a-technology/125-dr-abera-molla][http://dagmawibelete.blogspot.com/2013/05/ethiopic.html] [http://web.archive.org/web/20120202012912/http://www.ethiopic.com/ethiopic_computerization.htm]
[http://web.archive.org/web/20120202043306/http://www.ethiopic.com/unicode/Ethiopic_Computerization_in_Amharic.htm] [http://web.archive.org/web/20130104175325/http://www.ethiopic.com/Dr._Aberra_Molla_Ethiopic.htm] ለምሳሌ ያህል ፊደላቱ ከተበተኑበት ስምንት ፎንቶች ሌላ ድርብርብ ሆነው ከቀረቡት ሌሎች ፊደላት ኣንዱ የሞዴት መጻፊያ ፎንት መነሻ ዓማርኛ በብዛት የሚጠቀምበት ሳድሳኑ በቀዳሚነትና በብዛት ሁለተኛ የሆኑት የግዕዝ ቤት ቀለሞች በዝቅ መርገጫዎች እንዲከተቡ ቀርበዋል። ለስድስተኛ ምሳሌ ያህል የኮምፕዩተር የእንግሊዝኛ ምልክቶች ኣጠቃቀም ለግዕዙም እንዲያገለግል በተመጣጣኝ ቀለሞች ቀርበዋል። የእንግሊዝኛው ኣመዳደብ የተመረጠው የቍልፎች መለጠፊያዎች በሰባተኛነት ቢሠ’ሩም ግዴታ በመሆን እንዳያስፈልጉና [http://web.archive.org/web/20121225024954/http://www.ethiopic.com/overlay.htm] ኣከታተቡን ወደ እንግሊዝኛው QWERTY (ቅውኽርትይ) ገበታ ለማቀራረብ ነበር። በኮምፕዩተር ዘመን ግዕዝን ብቻውን ማቅረብ በቂ ስለኣልሆነ ግዕዙ የቀረበው በዘጠኝነት ከእንግሊዝኛ ፊደሎች ጋር ነው። ስለዚህ እንደ [[ግዕዝኤዲት]] ዩኒኮድ የኣሉት የ[[ሞዴት]]፣ [[ኢትዮወርድ]] እና ግዕዝኤዲት ፊደሎቻችን የእየእራሳቸው የእንግሊዝኛና የግዕዝ ፊደሎች ኣሏቸው። በዘጠኝነት ሕዝቡ እራሱን ኣከታተቦች እንዲያስተምር ጠቅሟል። በኣሥረኝነት የተጠቃሚዎች ቋንቋዎች ብዛት ተመጣጥነዋል፣ ስሕተቶችና ግድፈቶች እንዲታረሙና ወደ ዘመናዊ ኣሠራር እንዲሻሻሉ ሓሳቦች ቀርበዋል። በኣሥራ ኣንደኝነት ኣንድን ጽሑፍ በኣልተቀጠሉት የታይፕራይተር ገበታና በእንግሊዝኛ ዓይነት ኣቀማመጥ በሁለቱም ኣከታተብ መጻፍና ማሻሻል ቀርቶ በእንግሊዝኛው ዓይነት ብቻ እንዲሠራ ኣድርገዋል። በኣሥራ ሁለተኝነት ኣሠራሩም ለዘመናት የተለመዱትን የእንግሊዝኛ ዘዴዎችና ኣጠቃቀሞች ለግዕዙም በማድረግ ከኮምፕዩተር ወደ እጅ ስልኮች እንዲዘልቅ ሆኗል። የዶክተሩ ግኝት ለግዕዝ ብቻ ስለኣልሆነ እንግሊዝኛውንም ይመለከታል። በኣሥራ ሦስተኝነት ኣንድን ጽሑፍ ታይፕራይተርና በእንግሊዝኛው ኣጻጻፋቸው የተለያዩ ሰዎች እንዲከትቡና አንዲያሻሽሏቸው ኣስችለዋል። በመጨረሻም ዶክተሩ በፊደል ቅነሳ ባይስማሙም ለሚፈልጉት የተቀነሱትን የፊደል ገበታ ኣቅርበዋል። በኣሥራ ኣራተኛነት የዜሮ ኣኃዝ በሕንዶች ከሺህ ዓመታት ግድም ተገኝቶ ቀስ በቀስ ዓለም ሲጠቀምበት ኢትዮጵያውያን ምንም ሳያደርጉ ቆይተው በመጨረሻው የኣረቡን መጠቀም ስለጀመሩ ዶክተሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የግዕዝን ኣልቦዎች ፈጥረው ፊደሉ ከኮምፕዩተር ቴክኖጂሎጂ ጋር የሚሄድ ኣኃዛዊ ኣድርገውታል።
 
እንዲህም ሆኖ ግዕዝን በኮምፕዩተር መጠቀም ፊደሉን ማቅረብ የሚመስሏቸው ኣሉ። የላቲንም ሆነ የግዕዙ ፊደል መሣሪያው ላይ ከሌለ ሳጥን የመሰሉ ነገሮች ይታያሉ። ፓተንት የሚሰጠውም ለፊደሉ ወይም ፊደሉን ለሠራው ኣይደለም። የዶክተሩን ፊደላት መርገጫዎች ስፍራ ቀይሮ ማቅረብ ሕዝቡን ለማወናበድ እንጂ ኣዲስ ግኝት ወይም ገበታ ኣይደለም። የዶክተሩን ፈር ቀዳጅ ሥራ በተለያዩ ደካማ ገልባጮች መተካት ቢሞከርም ብቸኛውና ትክክለኛ በመሆን ከ፴፪ ዓመታት በላይ ማገልገሉን ቀጥሏል። ዶክተሩ መክተቢያዎቹን ወደ ኣንድ ሲያሻሽሉት ገልባጮች ከሁለት በላይ መርገጫዎችን በመጠቀም ያልተሟሉና ያልተከተቡ ጽሑፎችን በማቀረብ ሕዝቡን በማጃጃል ገፍተውበታል።