ከ«2019-20 ኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
→ቫይረሱ የሚገኝባቸው አገራት: ቁጥሮች ዘምነዋል። |
ቁጥሮች ዘምነዋል። |
||
መስመር፡ 1፦
የ2019-20 ኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ከባድ እና አጣዳፊ የመተንፈሻ አካላት በሽታ አምጪ በሆነው SARS-CoV-2 ቫይረስ ምክንያት የተከሰተ የኮሮናቫይረስ በሽታ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ ነው። ወረርሽኙ ለመጀመርያ ጊዜ የተገኘው በቻይና ዉሃን ሁቤ ውስጥ በእ.ኤ.አ. ዲሴምበር 2019 ነበር። [[የአለም ጤና ድርጅት|የዓለም ጤና ድርጅት]] በእ.ኤ.አ. ማርች 11 ቀን 2020 በሽታውን የወረርሽኝ ደረጃ ላይ መድረሱን አወጀ። እስከ መጋቢት
ልክ እንደ ኢንፍሉዌንዛ የቫይረሱ ዋነኛ መተላለፊያ መንገድ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ሲያስሉ ወይም ሲያስነጥሱ ከሚረጩ ፈሳሾች ነው። በሽታው ተላላፊ ነው ተብሎ የሚወሰደው ሰዎች የበሽታውን ምልክቶች በሚያሳዩበት ወቅት ቢሆንም አንድ አንድ ጊዜ ምልክቱን የማያሳዩ ሰዎች በሽታውን ሊያስተላልፉ ይችላሉ። አንድ ሰው ለቫይረሱ ከተጋለጠ በኋላ በአማካይ በአምስት ቀን ውስጥ ምልክቶችን ማሳየት ይጀምራል። ነገር ግን ምልክቱ እስኪታይ እስከ ዐሥራ አራት ቀን የሚቆይበት ሁኔታ አለ። የተለመዱት ምልክቶቹ ትኩሳት ፣ ሳል እና የትንፋሽ መቆራረጥ ናቸው። በሽታው ሲባባስ የሣንባ ምች እና የተለያዩ የመተንፈሻ አካላት በሽታዎችን ሊያስከትል ይችላል። በአሁኑ ጊዜ በሽታው ክትባት ወይም የጸረ-ቫይረስ ህክምና የለውም። በሽታውን ለመከላከል እጅን መታጠብ ፣ ሲያስሉ እና ሲያስነጥሱ አፍን መሸፈን ፣ በሽታው ካለባቸው ሰዎች ራቅ ማለት እናም በሽታው ካለባቸው ሰዎች ጋር ግንኙነት ከነበረ ራስን ለ14 ቀናት ማግለል ይመከራል።
|