ከ«የሐዋርያት ሥራ ፮» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
መስመር፡ 4፦
[[File:Van Dyck - The Stoning of Saint Stephen, 1623-1625.jpg|150px|thumb|የቅዱስ እስጢፋኖስ ወግረት]]
}}
የሐዋርያት ሥራ ፮ በአዲስ ኪዳን ፭ኛ መጽሐፍ "የሐዋርያት ሥራ" ውስጥ የሚገኝ ሲሆን "ስድስተኛው ምዕራፍ" ነው ። የሚያተኩረውም በቀዳሚ ሰማዕት ቅዲስ እስጢፋኖስ የመንፈሳዊ ተጋድሎ ሥራዎች ላይ ነው ። ይህም በ፵በ፲፭ ንዑስ ክፍሎች ይካተታል ።
 
<span style=font-size:16px>'''የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፮'''</span>
== ቁጥር ፩ - ፲፭ ==
1፤በዚህም፡ወራት፡ደቀ፡መዛሙርት፡እየበዙ፡ሲኼዱ፡ከግሪክ፡አገር፡መጥተው፡የነበሩት፡አይሁድ፡በይሁዳ፡
ኖረው፡በነበሩት፡አይሁድ፡አንጐራጐሩባቸው፥በየቀኑ፡በተሠራው፡አገልግሎት፡መበለቶቻቸውን፡ችላ፡
ይሉባቸው፡ነበርና።
2፤ዐሥራ፡ኹለቱም፡ደቀ፡መዛሙርት፡ዅሉን፡ጠርተው፡እንዲህ፡አሏቸው፦የእግዚአብሔር፡ቃል፡ትተን፡
ማእዱን፡እናገለግል፡ዘንድ፡የሚገ፟ባ፟፡ነገር፡አይደለም።
3፤ወንድሞች፡ሆይ፥በመልካም፡የተመሰከረላቸውን፡መንፈስ፡ቅዱስና፡ጥበብም፡የሞላባቸውን፡ሰባት፡ሰዎች፡
ከእናንተ፡ምረጡ፥ለዚህም፡ጕዳይ፡እንሾማቸዋለን፤
4፤እኛ፡ግን፡ለጸሎትና፡ቃሉን፡ለማገልገል፡እንተጋለን።
5፤ይህም፡ቃል፡ሕዝብን፡ዅሉ፡ደስ፡አሠኛቸው፤እምነትና፡መንፈስ፡ቅዱስም፡የሞላበትን፡ሰው፡
እስጢፋኖስን፡ፊልጶስንም፡ጵሮኮሮስንም፡ኒቃሮናንም፡ጢሞናንም፡ጳርሜናንም፡ወደ፡ይሁዲነት፡ገብቶ፡የነበረውን፡
የአንጾኪያውን፡ኒቆላዎስንም፡መረጡ።
6፤በሐዋርያትም፡ፊት፡አቆሟቸው፥ከጸለዩም፡በዃላ፡እጃቸውን፡ጫኑባቸው።
7፤የእግዚአብሔርም፡ቃል፡እየሰፋ፡ኼደ፥በኢየሩሳሌምም፡የደቀ፡መዛሙርት፡ቍጥር፡እጅግ፡እየበዛ፡
ኼደ፤ከካህናትም፡ብዙ፡ሰዎች፡ለሃይማኖት፡የታዘዙ፡ኾኑ።
8፤እስጢፋኖስም፡ጸጋንና፡ኀይልን፡ተሞልቶ፡በሕዝቡ፡መካከል፡ድንቅንና፡ታላቅ፡ምልክትን፡ያደርግ፡ነበር።
9፤የነጻ፡ወጪዎች፡ከተባለችው፡ምኵራብም፡ከቀሬናና፡ከእስክንድርያም፡ሰዎች፡ከኪልቅያና፡ከእስያም፡
ከነበሩት፡አንዳንዶቹ፡ተነሥተው፡እስጢፋኖስን፡ይከራከሩት፡ነበር፤
10፤ይናገርበት፡የነበረውንም፡ጥበብና፡መንፈስ፡ይቃወሙ፡ዘንድ፡አልቻሉም።
11፤በዚያን፡ጊዜ፦በሙሴ፡ላይ፡በእግዚአብሔርም፡ላይ፡የስድብን፡ነገር፡ሲናገር፡ሰምተነዋል፡የሚሉ፡ሰዎችን፡
አስነሡ።
12፤ሕዝቡንና፡ሽማግሌዎችንም፡ጻፊዎችንም፡አናደዱ፥ቀርበውም፡ያዙት፡ወደ፡ሸንጎም፡አመጡትና፦
13፤ይህ፡ሰው፡በዚህ፡በተቀደሰው፡ስፍራ፡በሕግም፡ላይ፡የስድብን፡ነገር፡ለመናገር፡አይተውም፤
14፤ይህ፡የናዝሬቱ፡ኢየሱስ፡ይህን፡ስፍራ፡ያፈርሰዋል፡ሙሴም፡ያስተላለፈልንን፡ሥርዐት፡ይለውጣል፡ሲል፡
ሰምተነዋልና፥የሚሉ፡የሐሰት፡ምስክሮችን፡አቆሙ።
15፤በሸንጎም፡የተቀመጡት፡ዅሉ፡ትኵር፡ብለው፡ሲመለከቱት፡እንደ፡መልአክ፡ፊት፡ኾኖ፡ፊቱን፡አዩት።