ከ«የወፍ በሽታ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «የወፍ በሽታ በእንግሊዘኛው ደግሞ ጀውንዳይስ (jaundice) የሚባለው ራሱን የቻለ አንድ በሽታ ሳይሆን የብ...»
 
No edit summary
መስመር፡ 1፦
የወፍ በሽታ በእንግሊዘኛው ደግሞ ጀውንዳይስ (jaundice) የሚባለው ራሱን የቻለ አንድ በሽታ ሳይሆን የብዙ በሽታወች ምልክት ነው። የወፍ በሽታ የሚከሰተው በደማችን የሚገኜው ቢሊሩቢን (bilirubin) የተባለው ከሚካል ብዛትመጠን ሲጨምር ነው። ይህ ከሚካልም ለቆዳችንና ለአይናችን ነጭ ክፍል ቢጫ ወይም ቢጫማ አረንጛደ ቀለም ይሰጣቸዋል። ይህ ምልክት ብቻውን ወይም ከለሎች ምልክቶች ለምሳለ ማሳከክ፤ የሰገራ ቀለም ወደ ቢጫነት እና የሽንት ወደ ጥቁርነት መቀየር እና ሆድ ህመም በተለይም በቀኝ በኩል ጉበት እና ሃሞት ባሉበት አካባቢ ይገኙበታል። የወፍ በሽታ በሁሉም እድሚ ክልል (ከጨቅላ ህጻናት እስከ አዋቂወች) ያሉ ሰወችን ያጠቃል። የወፍ በሽታ በጨቅላ ህጻናት ላይ ብዙውን ጊዚ በተወለዱ በመጀመሪያው ሳምንት የሚከሰት ሲሆን የከፋ ጉዳትም አያደርስም።
የወፍ በሽታ ከቀላል እስከ ከባድ በሆኑ በሽታወች ምክኒያት ሊመጣ ይችላል። በጢነኛ ሠው ደም ውስጥ ያለው የቢሊሩቢን መጠን ከ፩ ሚግ/ደሊ (1mg/dL) ያነሰ ሲሆን ይህ ምልክት ባለባቸው ሰወች ግን በትንሹ ከ ፪ ነጥብ ፭ እስከ ፫ ሚግ/ደሊ ነው። በተጨማሪም ይህ ምልክት ጨቅላ ህጻናት ላይ ሲከሰት የቢሊሩቢን መጠን ከ ፭ሚግ/ደሊ ያላነሰ መሆኑን ያመለክታል።