ከ«ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
የ197.156.107.25ን ለውጦች ወደ Codex Sinaiticus እትም መለሰ።
Tag: Rollback
መስመር፡ 1፦
{{የንጉሥ መረጃ
ንገሰ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ ተስፋ ስለሴ አድያም ሰገድ
| ስም = ቀዳማዊ ፡ ዓፄ ፡ ኃይለ ፡ ሥላሴ
| ርዕስ = [[ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ|ንጉሠ ፡ ነገሥት ፡ ዘኢትዮጵያ]]
| ስዕል = Haile Selassie (1969).jpg
| የስዕል_መግለጫ = በ ፲፱፻፷፱ (1969) እ.ኤ.አ.
| ግዛት = ከ[[ጥቅምት ፳፫]] ቀን [[1923|፲፱፻፳፫]] እስከ ፡ [[መስከረም ፪]] ፡ ቀን ፡ [[1967|፲፱፻፷፯]] ዓ.ም.
| በዓለ_ንግሥ = ጥቅምት ፳፫ ቀን ፲፱፻፳፫ ዓ.ም.
| ቀዳሚ = [[ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ|ንግሥት ፡ ዘውዲቱ]]
| ተከታይ = ዓፄ ፡ [[አምሃ ሥላሴ|አምሃ ፡ ሥላሴ]] (በስደት)
| ባለቤት = [[መነን አስፋው|እቴጌ ፡ መነን]]
| ልጆች = ልዕልት ፡ ሮማንወርቅ <br> ልዕልት ፡ ተናኜወርቅ <br> ዓፄ ፡ አምሀ ፡ ሥላሴ <br> ልዕልት ፡ ዘነበወርቅ <br> ልዕልት ፡ ፀሀይ <br> ልዑል ፡ መኮንን <br> ልዑል ፡ ሣህለ ፡ ሥላሴ
| ሙሉ_ስም = ራስ ፡ ተፈሪ ፡ መኮንን
| ሥርወ-መንግሥት = [[ሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥት|ሰሎሞን]]
| አባት = ራስ ፡ መኮንን ፡ ወልደ ሚካኤል ፡ ወልደ መለኮት
| እናት = ወ/ሮ ፡ የሺመቤት ፡ አሊ
| የተወለዱት = ሐምሌ ፲፯ ቀን ፲፰፻፹፬ ዓ.ም.
| የሞቱት = ነሐሴ ፳፩ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም.
| የተቀበሩት =
| ሀይማኖት = የኢትዮጵያ ፡ ኦርቶዶክስ ፡ ክርስትና
}}
'''ቀዳማዊ ፡ ዓፄ ፡ ኃይለ ፡ ሥላሴ''' ('''ቀ.ኃ.ሥ.''') ከ[[ጥቅምት 23|ጥቅምት ፳፫]] ቀን [[1923|፲፱፻፳፫]] እስከ መስከረም ፪ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. ፡ የ[[ኢትዮጵያ]] ፡ ንጉሠ ፡ ነገሥት ፡ ነበሩ። ተፈሪ ፡ መኰንን ፡ [[ሐምሌ ፲፮]] ፡ ቀን ፡ [[1884|፲፰፻፹፬]] ዓ.ም. ፡ ከአባታቸው ፡ ከልዑል ፡ [[ራስ መኰንን]] ፡ እና ፡ ከእናታቸው ፡ ከ[[ወይዘሮ የሺ እመቤት|ወይዘሮ ፡ የሺ ፡ እመቤት]] ፡ [[ኤጀርሳ ጎሮ|ኤጀርሳ ፡ ጎሮ]] ፡ በተባለ ፡ የገጠር ፡ ቀበሌ ፡ [[ሐረርጌ]] ፡ ውስጥ ፡ ተወለዱ።
 
በ[[1899|፲፰፻፺፱]] ፡ የ[[ሲዳሞ]] ፡ አውራጃ ፡ አገረ ፡ ገዥ ፡ ሆኑ። በ[[1903|፲፱፻፫]] ዓ.ም. ፡ የ[[ሐረርጌ]] ፡ አገረ ፡ ገዥ ፡ ሆኑ። የሐረርጌ ፡ አገረ ፡ ገዥ ፡ ሲሆኑ ፣ በጣም ፡ ብዙ ፡ ሺህ ፡ ተከታዮች ፡ ነበሩዋቸውና ፡ [[ልጅ እያሱ|ልጅ ፡ እያሱ]]ን ፡ ከእንደራሴነት ፡ በኅይል ፡ እንዳያስወጡ ፤ እያሱም ፡ ተፈሪን ፡ ከሐረር ፡ አገረ ፡ ገዥነት ፡ እንዳይሽሯቸው ፡ የሚል ፡ ስምምነት ፡ ተዋዋሉ። ዳሩ ፡ ግን ፡ እያሱ ፡ ሃይማኖታቸውን ፡ ከ[[ክርስትና]] ፡ ወደ ፡ [[እስልምና]] ፡ እንደቀየሩ ፡ የሚል ፡ ማስረጃ ፡ ቀረበና ፡ ብዙ ፡ መኳንንትና ፡ ቀሳውስት ፡ ስለዚህ ፡ ኢያሱን ፡ አልወደዱዋቸውም ፡ ነበር። ከዚህም ፡ በላይ ፡ እያሱ ፡ ተፈሪን ፡ ከሐረር ፡ ከአገረ ፡ ገዥነታቸው ፡ ለመሻር ፡ በሞከሩበት ፡ ወቅት ፡ ስምምነታቸው ፡ እንግዲህ ፡ ተሠርዞ ፡ ተፈሪ ፡ ደግሞ ፡ ለወገናቸው ፡ ከስምምነቱ ፡ ተለቅቀው ፡ በዚያን ፡ ጊዜ ፡ እሳቸው ፡ እያሱን ፡ ከእንደራሴነት ፡ አስወጡ። እንግዲህ ፡ በ[[1909|፲፱፻፱]] ፡ ዓ.ም. ፡ መኳንንቱ ፡ [[ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ|ዘውዲቱ]]ን ፡ ንግሥተ ፡ ነገሥት ፡ ሆነው ፡ አድርገዋቸው ፡ ተፈሪ ፡ ደግሞ ፡ እንደራሴ ፡ ሆኑ። ከዚህ ፡ ወቅት ፡ ጀምሮ ፡ ተፈሪ ፡ በኢትዮጵያ ፡ ውስጥ ፡ ባለሙሉ ፡ ሥልጣን ፡ ነበሩ። በ[[መስከረም ፳፯]] ፡ ቀን ፡ [[1921|፲፱፻፳፩]] ፡ ዓ.ም. ፡ የንጉሥነት ፡ ማዕረግ ፡ ተጨመረላችው። በ[[1922|፲፱፻፳፪]] ዓ.ም ፡ ንግሥት ፡ ዘውዲቱ ፡ አርፈው ፡ ንጉሠ ፡ ነገሥት ፡ ሆኑና ፡ [[ጥቅምት ፳፫]] ፡ ቀን ፡ [[1923|፲፱፻፳፫]] ዓ.ም. ፡ ብዙ ፡ የውጭ ፡ ልዑካን ፡ በተገኙበት ፡ ታላቅ ፡ ሥነ-ሥርዓት ፡ ቅብዓ ፡ ቅዱስ ፡ ተቀብተው ፡ እሳቸውና ፡ ሚስታቸው ፡ [[እቴጌ መነን|እቴጌ ፡ መነን]] ፡ ዘውድ ፡ ጫኑ።
 
[[ስዕል:King.jpg|180px|thumb|ቀዳማዊ ፡ ዓፄ ፡ ኃይለ ፡ ሥላሴ ፤ ንጉሠ-ነገሥት ፲፱፻፳፫ - ፲፱፻፷፮]]
 
በንግሥ ፡ በዓሉ ፡ ዋዜማ ፡ [[ጥቅምት ፳፪]] ፡ ቀን ፡ የትልቁ ፡ ንጉሠ-ነገሥት ፡ የ[[ዳግማዊ ምኒልክ|ዳግማዊ ፡ ዓፄ ፡ ምኒልክ]] ፡ ሐውልት ፡ በ[[መናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ|መናገሻ ፡ ቅዱስ ፡ ጊዮርጊስ]] ፡ ቤተ-ክርስቲያን ፡ አጠገብ ፤ ለዘውድ ፡ በዓል ፡ የመጡት ፡ እንግዶች ፡ በተገኙበት ፡ ሥርዐት ፣ የሐውልቱን ፡ መጋረጃ ፡ የመግለጥ ፡ ክብር ለ[[ዩናይትድ ኪንግደም|ብሪታንያ]] ፡ ንጉሥ ፡ ወኪል ፡ ለ(ዱክ ፡ ኦፍ ፡ ግሎስተር) ፡ ተሰጥቶ ፡ ሐውልቱ ፡ ተመረቀ።
 
ለንግሥ ፡ ስርዐቱ ፡ ጥሪ ፡ የተደረገላቸው ፡ የውጭ ፡ አገር ፡ ልኡካን ፡ ከየአገራቸው ፡ ጋዜጠኞች ፡ ጋር ፡ ከ[[ጥቅምት ፰]] ፡ ቀን ፡ ጀምሮ ፡ በየተራ ፡ ወደ ፡ [[አዲስ አበባ|አዲስ ፡ አበባ]] ፡ ገብተው ፡ ስለነበር ፡ ሥርዓቱ ፡ በዓለም ፡ ዜና ፡ ማሰራጫ ፡ በየአገሩ ፡ ታይቶ ፡ ነበር። በተለይም ፡ በ[[ዩናይትድ ኪንግደም|ብሪታንያ]] ፡ ቅኝ ፡ ግዛት ፡ በ[[ጃማይካ]] ፡ አንዳንድ ፡ ድሀ ፡ ጥቁር ፡ ሕዝቦች ፡ ስለ ፡ ማዕረጋቸው ፡ ተረድተው ፡ የተመለሰ ፡ [[መሢህ]] ፡ ነው ፡ ብለው ፡ ይሰብኩ ፡ ጀመር። እንደዚህ ፡ የሚሉት ፡ ሰዎች ፡ እስከ ፡ ዛሬ ፡ ድረስ ፡ ስለ ፡ ፊተኛው ፡ ስማቸው ፡ «ራስ ፡ ተፈሪ» ፡ ትዝታ ፡ ራሳቸውን ፡ «ራስታፋራይ» ፡ ([[ራሰተፈሪያውያን]]) ፡ ብለዋል።
 
ዓጼ ፡ ኃይለ ፡ ሥላሴ ፡ ዘውድ ፡ እንደጫኑ ፡ የአገሪቱን ፡ የመጀመሪያ ፡ [[ሕገ መንግሥት|ሕገ-መንግሥት]] ፡ እንዲዘጋጅ ፡ አዝዘው ፡ በዘውዱ ፡ አንደኛ ፡ ዓመት ፡ በዓል ፡ [[ጥቅምት ፳፫]] ፡ ቀን ፡ [[1924|፲፱፻፳፬]] ፡ ዓ.ም. ፡ በአዲሱ ፡ ምክር ፡ ቤት ፡ (ፓርላማ) ፡ ለሕዝብ ፡ ቀረበ። ከዚህም ፡ በላይ ፡ ብዙ ፡ የቴክኖዎሎጂ ፡ ስራዎችና ፡ መሻሻያዎች ፡ ወደ ፡ ኢትዮጵያ ፡ ከውጭ ፡ አገር ፡ አስገቡ።
 
በ[[1928|፲፱፻፳፰]] ዓ.ም. ፡ የ[[ሙሶሊኒ]] ፡ [[ፋሺስት]] ፡ ሠራዊት ፡ ኢትዮጵያን ፡ በወረረ ፡ ጊዜ ፡ ጃንሆይ ፡ ሕዝባቸውን ወራሪውን በሙሉ ለመቃወም እንዳስነሡና የከተት ዐዋጆቻቸው በታሪክ ገጾች ይዘገባሉ። በዐዋጅ መሠረት የዘመቻው ጊዜ እስቲያልቅ ድረስ ለሚታግሉ ነጋዶች ከ[[ቀረጥ]] አስተስርየት ሰጣቸው። እራሳቸው በቆራጥነት ፡ ከታገሉ ፡ በኋላ ፡ የጠላቱ ፡ ጦር ፡ ኅይል ፡ ግን ፡ በመጨረሻ ፡ ወደ ፡ እንግሊዝ ፡ አገር ፡ ለጊዜው ፡ አሰደዳቸው። ወደ ፡ [[ጄኔቭ]] ፡ [[ስዊስ]] ፡ ወደ ፡ [[ዓለም መንግሥታት ማኅበር|ዓለም ፡ መንግሥታት ፡ ማኅበር]] ፡ ሄደው ፡ ስለ ፡ ጣልያኖች ፡ የዓለምን ፡ እርዳታ ፡ በመጠየቅ ፡ ተናገሩ። የዓለም ፡ መንግሥታት ፡ ግን ፡ ብዙ ፡ አላደረጉም። በ[[1932|፲፱፻፴፪]] ዓ.ም. ፡ ግን ፡ [[አውሮፓ]] ፡ ሁሉ ፡ በ[[ሁለተኛው የዓለም ጦርነት|ሁለተኛው ፡ የዓለም ፡ ጦርነት]] ፡ ተያዘ። የእንግሊዝ ፡ ሠራዊቶች ፡ ለኢትዮጵያ ፡ [[አርበኞች]] ፡ እርዳታ ፡ በመስጠት ፡ ጣልያኖች ፡ ተሸንፈው ፡ በ[[1933|፲፱፻፴፫]] ዓ.ም. ፡ ኢትዮጵያን ፡ ተዉ። ዓፄ ፡ ኃይለ ፡ ሥላሴ ፡ አዲስ ፡ አበባን ፡ እንደገና ፡ የገቡበት ፡ ቀን ፡ ከወጡበት ፡ ቀን ፡ በልኩ ፡ ዕለት ፡ አምስት ፡ ዓመት ፡ በኋላ ፡ ነበረ።
 
[[ስዕል:ተፈሪ1892.jpg|200px|left|thumb| ልጅ ፡ ተፈሪ ፡ መኮንን ፡ በ፲፰፻፺፪ ዓ.ም.]]
ከዚህ ፡ በኋላ ፡ [[በ1948 ዓ.ም. ተሻሽሎ የወጣ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት]] ፡ የሕዝቦችን ፡ መብቶችና ፡ ተከፋይነት ፡ በመንግሥት ፡ አስፋፍቶ ፡ ሁለቱ ፡ ምክር ፡ ቤቶች ፡ እንደመረጡ ፡ አደረገ። በ[[1955|፲፱፻፶፭]] ዓ.ም. ፡ ግርማዊነታቸው ፡ [[የአፍሪካ አንድነት ድርጅት|የአፍሪካ ፡ አንድነት ፡ ድርጅት]] ፡ በአዲስ ፡ አበባ ፡ እንዲመሠረት ፡ ብዙ ፡ ድጋፍ ፡ ሰጡ። በ[[1958|፲፱፻፶፰]] ዓ.ም. ፡ ወደ ፡ ካሪቢያን ፡ ጉብኝት ፡ አድርገው ፡ የጃማይካ ፡ ራስታዎች ፡ ተገኛኙ። በ[[1967|፲፱፻፷፯]] ዓ.ም. ፡ በ[[ማርክሲስት]] ፡ አብዮት ፡ [[ደርግ]] ፡ ሥልጣን ፡ ያዙና ፡ እሳቸው ፡ በእሥር ፡ ቤት ፡ ታሰሩ። በሚከተለው ፡ ዓመት ፡ ከተፈጥሮ ፡ ጠንቅ ፡ እንደ ፡ አረፉ ፡ አሉ ፤ ሆኖም ፡ ለምን ፡ እንደ ፡ ሞቱ ፡ ስለሚለው ፡ ጥያቄ ፡ ትንሽ ፡ ክርክር ፡ አለ። ብዙ ፡ ራስታዎች ፡ ደግሞ ፡ አሁን ፡ እንደሚኖሩ ፡ ይላሉ።
 
== ስያሜያቸው==