ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 130፦
ኢትዮጵያውያን ስለ [[ሄኖክ]] ዘመን ኣቈጣጠርም ያውቃሉ። [http://www.timeemits.com/FAQs_11-1-8.htm] የሄኖክ ዓመት 364 ቀናት ነበሩት። [http://www.timeemits.com/FAQs_11-1-8.htm] የኢትዮጵያ [[መጽሓፍ ቅዱስ]] ውስጥ መጽሓፈ ሄኖክ ምዕራፍ ፲፰ ቍጥር ፲፩ ስለ 364 የዓመት ቀናት ይናገራል።
 
ኢትዮጵያውያን ሲወርድ ሲወራረድ የመጣውን የነገሥታት የስም ዝርዝር ለብዙ ሺህ ዓመታት ከ[[ክርስቶስ ልደት በፊት]] 4,400 ዓመት በመጀመር ኣቆይተውልናል። ይህ ከ1,000 ዓመተ ዓለም ግድም ጀምሮ መሆኑ ነው። ይህ ኢትዮጵያውያን የእራሳቸው የዘመን መቍጠሪያ እንደነበራቸው የሚያመለክት ኣንድ ማስረጃ ነው። [https://www.facebook.com/permalink.php?story_fbid=1493709244261830&id=1451412358491519] [http://rastaites.com/HIM/lineage.htm] የግብጽና የሌሎችም እዚህ ኣለ። የጥንት ኢትዮጵያውያን የከዋክብትን ሳይንስ ፈጥረውና ስም ሰጥተዋቸው ለግብጻውያን ኣስተላለፉ ይባላል። [https://tseday.wordpress.com/2008/09/14/ethiopian-astronomy/] የግሪክ ፊደል ከግብጹ ዴሞቲክ የተወሰደ ነው ይባላል።
 
የኢትዮጵያ ዘመን ኣቈጣጠር (Ethiopian calendar) የጁልያን ዘመን ኣቈጣጠር ኣይደለም። [[ጁልየስ ሲዘር]] ባለ 10 ወራትና 300 ቀናት የነበረውን የሮማውያን ካላንደር ትቶ 365.25 ቀናት የኣለውን ካለንደር ወስዷል። በኣሁኑ ጊዜ በጁልያንና በጎርጎርዮስ ካለንደሮች መካከል ያለው የ13 ቀናት ልዩነት ሲሆን የዓመታቱ ቍጥሮች ግን (2017) ልዩ ኣይደሉም። በ525 ዓ.ም. [[ዲኖስዮስ ኤክሲጅዮስ]] (Dionysius Exiguus) የሚባል የሩስያ መነኩሴ የሮማው ጳጳስ መልዕክተኛም በመሆን የፋሲካን በዓል ኣወሳሰን ከግብጻውያን እንዲማር ተልኮ ነበር። እንደሚመስለኝና ኣንዳንድ ፀሓፊዎችም እንደሚሉት ኤክሲጅዮስ በ525 ዓ.ም. 532 ዓመትን ሳይጠቀም ኣልቀረም። ዲኖስየስ ኣኖ ዶሚኒ (Anno Domini ወይም ኤ.ዲ.) የሚባለውን ካለንደር በጃንዋሪ 1፣ 1 ኤ.ዲ. እንዲጀምር በ525 ቢወስንም በኋላም ፀሓፊዎች ጁልያን (ዩልዮስ) ካለንደር የኣሉት የግብጾችንና የኢትዮጵያን ዘመን መቊጠርያዎች ስለማይመለከት እራሱን የቻለ ካለንደር ሆኖ ቆይቷል። ኤክሲጅዮስ ወደኋላ በመቍጠር ሲጀምር ይመስለኛል ኣዲሱ ካለንደር ላይ ሰባት ዓመታት ግድም የጨመረበት ይላሉ ዶክተር ኣበራ ሞላ። የዓመታቱም ቍጥር ከግብጽ ይልቅ ወደ ኢትዮጵያ የቀረበ ነው። ምክንያቱም የግብጻውያን ዓመተ ሰማዕታት ኣንድ ብሎ በ፪፻፸፮ ዓ.ም. የጀመረ ስለሆነ ነው። [https://ethiopiancalendar.wordpress.com/history/] ጨረቃ መሬትን ስትዞርና መሬት ፀሓይን ስትዞር የሚወስዱት 532 ዓመታት (19 X 28) ተደጋጋሚነታቸው የታወቁ ናቸው በማለት ዶክተሩ ጽፈዋል። [https://web.archive.org/web/20100105030957/http://www.ethiopic.com/unicode/The_Ethiopian_Calendar_in_Amharic.htm] [http://archive.is/hKHz#selection-2983.2-2987.164] [http://www.danielkibret.com/2014/09/blog-post_5.html] [http://am.sciencegraph.net/wiki/%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB_%E1%8B%98%E1%88%98%E1%8A%95_%E1%8A%A0%E1%89%86%E1%8C%A3%E1%8C%A0%E1%88%AD] ኣሁን ያለነው ፲፭ኛው የ፭፻፴፪ ዓመታት ዙር ውስጥ ነው። የዲኖስዮስ ጁልያን ካላንደር ስሕተት እንደነበረው የቫቲካኑ ጳጳስ በቅርቡ በመጽሓፋቸው ስለኣሰፈሩ ዶክተሩም ኣመስግነዋቸዋል። [http://ethiopianamericanforum.com/index.php?option=com_content&view=article&id=405:christian-calendar][http://www.ethiomedia.com/assert/4848.html] ምክንያቱም የዩልዮስ ቀለንጦስ ተጠቃሚዎች የኢትዮጵያው ላይ ሰባት ዓመታት ግድም ቢጨመሩም የእኛው ወደ ትክክለኛው የቀረበ ሳይሆን ኣልቀረም።