ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
መስመር፡ 478፦
፩. ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ ዶክተሩ የቁምፊውን መጠን በግምት ኣስቀመጡት እንጂ መደብ ኣላወጡለትም። ፪. በኣሁኑ ጊዜ ሕዝቡ በግዕዝ ፊደል በብዛት መጽሓፍት እየጻፈ ስለሆነ እየተደሰትን ነው። ሆኖም ጽሑፎች እየታተሙባቸው የኣሉት ቁምፊዎች መልኮች የተለያዩና ኣብዛኛዎቹ የተሳሳቱ ስለሆኑ መጠንቀቅ ያስፈልጋል። ከግዕዝኤዲት ፕሮግራሞች ጋር እየተሸጠ የኣለው የዶ/ር ኣበራ ሞላ ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ (GeezEdit Unicode) ቁምፊ ወደ ትክክለኛው የቀረበ ነው። [http://archive.fo/uKbLy] ይኸን ቁምፊ ከተጠቀሙበት መካከል ዶ/ር ኣክሊሉ ሃብቴ በ፳፻፱ ዓ.ም. ያሳተሙት ባለ 629 ገጾች "የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ታሪክ" መጽሓፍ ኣንዱ ነው። [http://quatero.net/amharic1/archives/28975] በፊደሉ ለብዙ ዓመታት እየተጠቀሙበት የኣሉት የኣቶ ኣብርሃ በላይ ኢትዮሚዲያ ገጾችም ኣሉ። [http://www.ethiomedia.com/1000bits/the-works-of-dr-aberra-molla.pdf] በ፳፻፲፩ ዓ.ም. ሰይፉ ኣዳነች ብሻው በግዕዝኤዲት ፕሮግራም በመጠቀም "የምኒልክ ጥላ" መጽሓፍ ጽፈዋል። በጽሑፋቸውም ዶክተር ኣበራ ስለ ሆኄያት መልኮች በተለይ የ"ጨ" ባሁለት እግርነት እውነታ ተቀብለዋል። ፫. መጽሓፍ በኮምፕዩተር ሲታተም ቁምፊውን ኣስቀድሞ መወሰን ይጠቅማል። ምክንያቱም በኣንድኣንድ ኣስቀያሚና የተሳሳቱ የፊደል መልኮች የተጻፉ ጽሑፎች ማንበብ ኣያጓጓም። [http://www.dallascounty.org/department/hhs/documents/DCHHS_ZikaVirus_FactSheet_Amharic_Feb2016.pdf] ፬. ኣንድ የግዕዝ ዩኒኮድ ቁምፊ ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች እንደኣሉት ማጣራት የደራሲው ሥራ ነው። ምክንያቱም ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው የማተሚያ ቤቶቹን ኃላፊነት ለደራሲዎች ስለሰጡ ኣዲሱን ቴክኖሎጂ መማር ኣስፈላጊ ስለሆነ ነው።
፭. ኣንድ በግዕዝ ዩኒኮድ ቁምፊ የሚጠቀም ደራሲ ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች መክተብ መቻሉን ማጣራት የደራሲ ሥራ ነው። ምክንያቱም ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው የማተሚያ ቤቶቹን ኃላፊነት ለደራሲዎች ስለሰጡ ኣዲሱን ቴክኖሎጂ መማር ኣስፈላጊ ስለሆነ ነው። ፮. ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ ዶክተሩ በመደበኛነት (Standard) የተጠቀሙት የኢትዮጵያ ቍጥር ፩ ፊደል ነው። እ.ኤ.ኣ. በ1988 በዶክተሩ ከፖስትእስክሪፕት (Postscript) ፊደላቸው የተሠራ የመጀመሪያው ትሩታይፕ (TrueType) የግዕዝ ፊደልና ፊደላቸው ነው። ለሥራቸው መሳካት የኮሎራዶው ኩባንያዎች ከዶክተሩ ባለውለታዎች ዋነኞቹ ናቸው። ይህ እነ ብርሃንና ሰላምና የመሰሉ የኢትዮጵያ ማተሚያ ቤቶች ሲጠቀሙበት የነበረው ቁምፊ ወደ ታይምስ ሮማን (Times Roman) የእንግሊዝኛ ቁምፊ የቀረበና ተመሳሳይ ቢሆንም ከላቲኑ ጋር ሲወዳደር የግዕዝ ፊደል ተለቅና ደመቅ የኣለ ነው። [https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%88%9B%E1%88%AD%E1%8A%9B_%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%8C%8D%E1%88%8A%E1%8B%9D%E1%8A%9B_%E1%88%98%E1%8B%9D%E1%8C%88%E1%89%A0_%E1%89%83%E1%88%8B%E1%89%B5_1833] ኣብዛኛዎቹ የዓማርኛና እንግሊዝኛ መጽሓፍት ሲጻፉ የነበሩት በእነዚህ ቁምፊዎች ነበር። ይህ የግዕዝ ቁምፊ መልክ ወደጎን ቀጠን ብሎ ወደታች የወፈረ ነው። በማተሚያ ቤቶቹና ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ ሲታተሙ የነበሩት መጽሓፎች የፊደል መጠን (Points) ከ10 እስከ 12 ነበር። ፰. ኣንድ የግዕዝ ቁምፊ ቢያንስ ከኣንድ ተመጣጣኝ የእንግሊዝኛ ቁምፊ ጋር መቅረብ ይኖርበታል።
፱. ኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች ላይ በቀላሉ ማየት እንዲቻል የሚቀርቡ ጽሑፎች ደቦልቦል በኣሉ ቁምፊዎች ነው። እነዚህን ለመጽሓፎችና ለመሳሰሉት መጠቀም ኣስፈላጊ ኣይደለም። ምክንያቱም ትላልቅ ስለሆኑ በዛ የኣሉ ስፍራዎችንና ወረቀቶችን ስለሚያስባክኑና ጥቅማቸው ለኅትመት ስለኣልሆነ ነው። ፲. ኣንዳኣንድ ሰዎች ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ማድረግ ፊደሉን መሥራትና ማቅረብ ይመስላቸዋል። ይህ ከኣለማወቅ የመጣ ስሕተት ነው። በፓተንት የሚጠበቀው ኣዲስ የሆነውና ፊደሉን በኮምፕዩተር መጠቀም የኣስቻለውን ቀደም ብሎ ያልነበረውን ዘዴ ነው እንጂ ከዘዴው ጋር ለሚቀርቡት ፊደላት ኣይደለም። ፲፩. ኣንዳኣንድ ሰዎች ግዕዝን ኣሜሪካ ፓተንት ማድረግ ፓተንቱን ወይም ፊደሉን ለኣሜሪካ መስጠት ይመስላቸዋል። ይህ ከኣለማወቅ የመጣ የፈጠራ ወሬ ነው። ፲፪. ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው ከትክክለኛው ቁምፊ ጋር ዶክተሩ ከኣቀረቡ በኋላ ከአማርኛው ቅጥልጥል ፊደል እስከኣልተሟሉና የተሳሳቱ ቀለሞች የኣሉዋቸውን ቁምፊዎች በነፃና በሽያጭ የሚያቀርቡ ኣሉ። ይኸንን መረዳትና ማስተዋል የተጠቃሚው ኃላፊነት ሲሆን ኣንባቢው ስሕተቶችን እያየ ዝም ማለቱ ደረጃቸው ለኣዘቀጡ በኮምፕዩተር ለቀረቡ ጽሑፎች ኣስተዋጽዖ እያበረከተ ነው።
|