ከ«ወሎ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Added content
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Added English name
Tags: Visual edit በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 1፦
'''ወሎ''' (Wollo) በሰሜን ምስራቅ የ[[ኢትዮጵያ]] ክፍል የሚገኝ ታሪካዊ አውራጃ እና ክፍለ ሀገር ሲሆን ዋና ከተማዋ [[ደሴ]] ነው። ከ1700ዓም በፊት ከፊል የወሎ አካል ስሙ ''' አምሐራ ''' የነበረ ሲሆን [[17ኛው ክፍለ ዘመን]] የ[[ኦሮሞ]] መስፋፋትን ተከትሎ በአከባቢዉ በፊት አምሐራ ተብሎ የሚጠራውን አካባቢ ጨምሮ ወሎ በሚባል ሰፊ ግዛት አካታች በሆነ ስያሜ እና ማንነት መጠራት ጀመረ ። ወሎ እንዳሁኑ በስፋት ከመዋሀዱ በፊት በቀድሞ ካርታዎች "አምሐራ" በሚል ስያሜ በሰሜን በሽሎ ወንዝ፣ በደቡብ ጃማ ወንዝ፣ በምእራብ አባይና በምስራቅ አፋር ያዋስኑት ነበር።
የወሎ ድንበር በየዘመኑ የመስፋት እና የመጥበብ ሁኔታዎች የሚታይበት ሲሆን በአንዳንድ የታሪክ አጋጣሚዎች እስከ [[አሰብ]] ድረስ ይሰፋ ነበር፡፡ ከ[[ጣልያን]] ጦርነት ቀጥሎ በ[[1933]] ዓ.ም. [[አዛቦ]]፣ [[ላስታ]]፣ [[ራያ]]፣ [[ዋግ]] እና [[የጁ]] ይፋዊ የወሎ ግዛቶች ሆኑ። ወሎ እጅግ ሰፊ የሚባል ጠቅላይ ግዛት የነበረ ሲሆን በስፋቱም ከሀረርጌ፣ ከባሌ እና ከሲዳሞ በመቀጠል በአራተኛ ደረጃ ላይ የቀመጣል ስፋቱም 79,4002 ስኩየር ኪሎሜትር ነበር፡፡
 
ከ «https://am.wikipedia.org/wiki/ወሎ» የተወሰደ