ከ«ቅዱስ ሩፋኤል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ Advanced mobile edit
መስመር፡ 9፦
 
የወላድ ማኀፀን እንዲፈታ ስለተሾመ ከጌታ አዋላጅ ብትኖርም ባትኖርም ሩፋኤል አይታጣም ፣ በምጥ ጊዜ ሴቶች ሁሉ በባላገር ያሉ መልኩን ያነግታሉ ማየ ጸሎቱንም ይጠጣሉ ቶሎም በፍጥነት ይወልዳሉ ።
 
== ድርሳነ ሩፋኤል ==
 
፩ ፤ በአብ ስም አምነን አብ ወላዲ ብለን በወልድ ስም አምነን ወልድን ተወላዲ ብለን በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነን መንፈስ ቅዱስን ሠራፂ ብለን ምንም ለአጠይቆ አካላት ሦስት ብለን በባሕርይ በሕልውና በመለኮት አንድ አምላክ ብለን አምነን አስቀድሞ በኅዳር ፲፪ ቀን እንደተናገርነው ክቡራን የሚሆኑ ከሰማያውያን ሊቃነ መላእክት ሦስተኛ የሚሆን የቅዱስ ሩፋኤል በዓለ ንግሥ በጳጉሜ ሦስት ቀን የሚከበርና የሚታሰብ መሆኑን እንናገራለን ።
 
፪ ፤ ይህም ዕለት በሊቀ ጳጳሱ በአባ ቴዎፍሎስ ዘመን እስክንድርያ በምትባል አገር ዳርቻ ባለች ደሴት በውስጧ ብዙ ተአምራት የተፈፀመባት በቅዱስ ሩፋኤል ስም የታነፀች ቤተ ክርስቲያን የተባረከችበትና የተቀደሰችበት ዕለት ነው ።
 
፫ ፤ ይህም የሆነው አንዲት በጣም ሀብታም የሆነች ሮማዊት የሮም ሀገር ሴት ንዑድ ክቡር የሚሆን የቅዱስ ሩፋኤልን ሥዕልና ልጆችዋን እንዲሁም ከባልዋ በውርስ ያገኘችውን ብዙ ገንዘብ ይዛ ወደ ሊቀ ጳጳሱ ወደ ቴዎፍሎስ ዘንድ በመጣችበት ጊዜ ነበር ።
 
፬ ፤ ከመጣችም በኋላ በሊቀ ጳጳሱ ቤት ፊት ለፊት ያለውን ኮረብታ አስቆፈረችና ከመሬት ውስጥ ወርቅ የተከማቸበት ሣጥን ተገኘ ።
 
፭ ፤ ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሱ አባ ቴዎፍሎስ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን አሣነፀ ከነዚህም ውስጥ እስክንድርያ በምትባል አገር ዳርቻ ባለች ደሴት ላይ ክቡር በሚሆን በቅዱስ ሩፋኤል ስም የተሠራች ቤተክርስቲያን ትገኝበት ነበር ሥራዋንም ሠርቶ በፈፀመ ጊዜ በዚችው ዕለት በታላቅ ክብር አክብሮ ባረካት ቀደሳትም ።
 
፮ ፤
[[መጽሐፈ ጦቢት]] ስለ ቅዱስ ሩፋኤል በሰፊው ያስተምራል በተለይ ጦቢት ፥ ፲፪-፲፭ ።