ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 401፦
 
፩. ጥንትም ቢሆን ፊደላት በእጅ ጽሑፍ ሲጻፉ ላቲን ከግዕዙ በፍጥነት የተከተበበት ጊዜ ኣልነበረም። ምክንያቱም ግዕዝ ኣንድን ድምጽ በኣንድ ቀለም ሲያሰፍር ለኣብዛኛው የላቲን ድምጾች ሁለት ቀለሞች ስለሚያስፈልጉት ነው። ፪. የላቲንና ግዕዝ ቀለሞች (ኦሮምኛውን ግዕዝ ጨምሮ) በማተሚያ መሣሪያዎች ሲከተቡ የሁለቱም ቀለሞች መረጣዎች ኣጠቃቀሞች እኩል ነበር። በእዚህ ዘዴ የኦሮምኛ ዓማርኛ መተርጐሚያ (Lexicon) በ1850 ግድም በኣቶ ሓብተ ሥላሴ ታትሟል። [https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A0%E1%8D%8B%E1%8A%95_%E1%8A%A6%E1%88%AD%E1%88%9B_%E1%88%9B_%E1%88%98%E1%8B%9D%E1%8C%88%E1%89%A0_%E1%89%83%E1%88%8B%E1%89%B5_1850] መጽሓፍ ቅዱስን ወደ ኦሮምኛ የመተርጐሙንም ሥራ በማስፋፋት ከሌሎች የቋንቋው ተናጋሪዎች ጋር (ዋሬ፣ ሩፎ፣ ሾለን፣ ጀገን እና ገብረሚካኤል) በመተባበር ሙሉውን ኣዲስ ኪዳን ወደ ኦሮምኛ ተርጕመው በሰኔ 1862 ዓ.ም. ኣገባደዱ። ይህም ትርጕማቸው ለኦሮምኛ ሥነጽሑፍ የመጀመሪያው ኣዲስ ኪዳን መሆኑ ነው። ከጥቂት ዓመታት በኋላም ሚስዮኑ ክራጵፍ ([[J.L. Krapf]]) በ፲፰፻፸፩ ዓ.ም. በራሱ ስም ያሳተመው ይህንኑ የነ[[ኣለቃ ዘነብ]]ን ፲፰፻፷፪ ዓ.ም. ሥራ “ቁልቁሎታ መጻፎታ ከኩ ሐረዋ” ነበር። [https://andemta.com/2017/06/26/%e1%8a%a0%e1%88%88%e1%89%83-%e1%8b%98%e1%8a%90%e1%89%a5/] ኣለቃ ዘነብ ወደ ፲፰፻፸ ዓ.ም. ግድም የ“ኦሮምኛና ኣገውኛ መዝገበ ቃላት” ጽፈዋል ይባላል። የ[[ኣስቴር ጋኖ]]ን የትርጕም መጽሓፍ በመጠቀም በ፲፰፻፹፯ ዓ.ም. የታተመም የኦሮምኛ [[ሓዲስ ኪዳን]]፣ [https://en.wikipedia.org/wiki/Aster_Ganno] [[መጫፈ ቁልቁሉ]] በ፲፰፻፺፱ እ.ኤ.ኣ. (፲፰፻፺፪ ዓ.ም.) በቅዱስ [[ኦነሲሞስ ነሲብ]]፣ [https://en.wikipedia.org/wiki/Onesimos_Nesib]
[https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%8A%A6%E1%8A%90%E1%88%B2%E1%88%9E%E1%88%B5_%E1%8A%90%E1%88%B2%E1%89%A5] እና ከእዚያም ወዲህ እንደነ [[በሪሳ]] የኣሉ ጋዜጣዎች በግዕዝ ፊደል በኦሮምኛ ታትመዋል። መጫፈ ቁልቁሉ ለመጀመሪያ ጊዜ በግዕዝ ፊደል በኦሮምኛ ቋንቋ የተጻፈ የፈረንጁ መጽሓፍ ቅዱስ ትርጕም ነው። ቀደም ብሎም በግዕዝ ፊደል በኦሮምኛ ከቀረቡት መረጃዎች ኣንዱ [[ጀምስ ብሩስ]] የወሰደው የ1790 የኦሮምኛ ትርጕምና የኢዘንበርግ ጽሑፍም ኣሉ። [https://m.facebook.com/photo.php?fbid=1066288513502794&id=100003649675444&set=a.749136815217967.1073741828.100003649675444&source=57] ፫. በዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝድ የሆነው ግዕዝ እ.ኤ.ኣ. በ1987 ለገበያ ቀርቦ በማተሚያ ቤቶች ፊደላት መክተብ ስለተጀመረ ምሁራን ደስ ሊላቸውና ሳይንሱንና ቴክኖሎጅውን ማወቅና ማስተዋወቅ በተገባ ነበር። ይህ በኣለመደረጉ እ.ኤ.ኣ. በ1992 [http://www.ethiopians.com/bayeyima.html] በፕሮፌሰር [[ጥላሁን ጋሜታ]] ወደ ላቲን ለማዞር ከቀረቡት የኣማርኛ የጽሕፈት መኪናን የሚመለከቱት ጊዜ ለኣለፈባቸው ምክንያቶች መልሶችም ነበሩ። [https://archive.li/WIjry] [http://sirius-c.ncat.edu/EAS/news/EJSciTech/abera2.html] [http://www.ethiopians.com/bayeyima.html] ስለዚህ በግዕዝ ፊደል በማተሚያ ፊደላት ሲጻፉ የነበሩት በኮምፕዩተር ስለቀረቡ ቴክኖሎጂው ስለተሻሻለና ስለቀለለ ጉዳዩ ይመለከተናል የኣሉት የኦሮሞ ምሁራን ሊደሰቱ የሚገባ እንጂ ወደ ላቲን የሚያስዞር ኣዲስ ምክንያት ኣልነበረም። በጊዜውም በፕሮፌሰር [[ባዬ ይማም]] በዓማርኛ መልስ ቀርቦ ፕሮፌሰር ሚንጋ ነጋሽና ፕሮፌሰር ሳሙኤል ክንዴ ወደ እንግሊዝኛ ተርጕመውታል። [http://www.ethiopians.com/bayeyima.html] ፬. ላቲን የእራሱ ችግሮች የኣሉት ፊደል ነው። [http://www.i18nguy.com/twain.html] [http://www.smart-jokes.org/english-spelling-reform.html] [https://www.youtube.com/watch?v=06JhqTexYsM] [https://www.theguardian.com/media/mind-your-language/2014/dec/11/mind-your-language-english-spelling] በዶክተሩ ግኝት እየኣንድኣንዱን የግዕዝ ቀለም በሁለት መርገጫዎች መክተብ ተችሏል። ላቲን ይኸን እየኣንዳንዱን የግዕዝ ቀለም በሁለት መርገጫዎች የመክተብ ችሎታ ስለሌለው ግዕዝን በግዕዝ ፊደል መክተብ ብልጫ ኣገኘ። ስለዚህ ኦሮምኛን በላቲን ፊደል መክተብ (ቁቤ) መሻሻል ኣይደለም።
 
፭. የኦሮምኛው የግዕዝ ፊደል ከሌሎቹ የግዕዝ ቀለሞች ጋር በዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ [http://archive.li/WIjry] ለኣለፉት ፴፪ ዓመታት በኮምፕዩተር ቀርቦ በኋላም በዩኒኮድ ዕውቅና ቢያገኝም [https://en.wikipedia.org/wiki/Ethiopic_(Unicode_block)] ሁሉም ባይሆኑ ኦሮሞዎች ግዕዙን እርግፍ ኣድርገው ጥለው ወደ ላቲኑ ስለዞሩ የተፈጠሩት ችግሮች ቀጥለዋል። ለምሳሌ ያህል ላቲን እራሱን የሚገልጸው የኮምፕዩተሩ ገበታ ላይ በኣሉት ቀለሞች ብቻ ኣይደለም። ፮. በእጅ የጽሕፈት መሣሪያ ዘመን ታይፕራይተር ዓማርኛንና ኦሮምኛን ለማስጻፍ ስለኣልቻለ ላቲን ብልጫ ነበረው። የዶክተሩ ግኝት ለእውሸቱ (የፈጠራ) የታይፕራይተር የኣማርኛ ነገሮችና ለትክክለኛዎቹ የማተሚያ ቤቶች ፊደላት ኣጠቃቀሞች እጅግ ትልቅ ፈውስ (Breakthrough) ነበር። የታይፕራይተር ፊደል ለታይፕራይተር ሲባል የተሠራ በፍፁም ትክክለኛ በኣለመሆኑና ለብዙ ምዕት ዓመታትም በእጅ ስንጽፈው የነበረው ከኣለመሆኑም ሌላ የማተሚያ ቤት ፊደላችንም ስለኣልሆነ ከቁርጥራጮች የሚሠራውን ብጥስጥስ ዶ/ር ኣበራ እውሸት ፊደል ይሉታል። ስለ ታይፕራይተሩ ድክመት ዶክተሩ እ.ኤ.ኣ. በ1991 [http://trigonal.ncat.edu/AAU-Network/news/EJSciTech/abera2.html] [https://www.facebook.com/notes/geezedit/advances-made-by-ethiopians-in-the-computer-technology-1991/403555123037729/] ስለኣቀረቡ መሣሪያው ወደ ቁቤ ለመዞር ምክንያት መሆን ኣልነበረበትም። ከእዚያም ወዲህ በኮምፕዩተር የኦሮምኛው የግዕዝ ፊደል በዶክተሩ መከተብ መቻልና የተጠቃሚዎች መኖር ግንዛቤ ውስጥ ሳይገቡ ብዙ ዓመታት ባክነዋል። ቴክኖሎጂ የችግር መፍቻ እንጂ ከችግር መሸሽያ ኣይደለም። ፯. ቁቤ በላቲን ዋየሎች ከሚጠቀምባቸው በተሻለ ኦሮምኛ በግዕዙ ሊጠቀም ይችላል። ኦሮምኛን በፊደል ለመክተብ ከላቲኑ ቁቤ የግዕዝ ፊደል ይጠቅማል። [https://www.youtube.com/watch?v=I97bJbKbW6w] [http://www.ethiomedia.com/1000bits/geez-for-qubee.html] [https://www.satenaw.com/amharic/archives/56312] ፰. መጽሓፍ ቅዱስ በከፊል እ.ኤ.ኣ. በ1841 በኦሮሞ ቋንቋ በግዕዝ ፊደል ተጽፏል። [http://www.worldscriptures.org/pages/oromocentral.html] [http://www.worldscriptures.org/pages/boranaoromo.html] እንዲሁም እ.ኤ.ኣ. በ1875 የኦሮሞ ሓዲስ ኪዳን በግዕዝ ፊደል ታትሟል። [http://www.worldscriptures.org/pages/oromoeastern.html] [https://web.archive.org/web/20160405073858/http://www.worldscriptures.org/pages/oromowestern.html] [https://web.archive.org/web/20160904072134/http://www.worldscriptures.org/pages/oromoeastern.html]