ከ«ውክፔዲያ:Current featured article» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
No edit summary |
||
መስመር፡ 1፦
<div style="display:inline-block; box-shadow:0.2em 0.2em 0.2em #333"><big><big>'''[[
-----
<div style = "border: 1px solid #FeFedf; float:right; background: transparent; padding: 2px 0px 2px 3px;"><div style="display:inline-block; box-shadow:0.2em 0.2em 0.2em #333">[[ስዕል:
</br><center><div style = "text-shadow:
</center> </div>
'''ዋንዛ''' (Cordia Africana) በ[[ኢትዮጵያ]] እንዲሁም በ[[አፍሪካ]] ሁሉ የሚበቅል፣ እስከ 30 ሜትር ርዝመት የሚደርስ ግዙፍ ዛፍ ነው። ከ[[ደጋ]] አየር ንብረት በስተቀር [[ቆላ]]ና [[ወይና ደጋ]] ለዚህ ዛፍ ተስማሚ ናቸው። ቢጫ ፍሬው ሲበስል ከመጣፈጡ የተነሳ ለምግብነት ያገለግላል። የዋንዛ ቅርንጫፍ የተንሰራፋ ስለሆነ፣ ሌሎች አትክልቶችን፣ ለምሳሌ እንደ [[ቡና]] ያሉትን፣ ከ[[ፀሐይ]] ለመከላከል ይረዳል። ጥላ መከታ ይሆናል።
[[ቀፎ]] ዛፉ ላይ በማስቀመጥ፣ [[ንብ|ንቦች]]ን ለማርባት በጣም አይነተኛ ዛፍ ነው፤ ምክንያቱም የዛፉ አበቦች መዓዛቸው መልካም ሲሆን መልካቸውም ዓይን ይስባል (በተለይ የንቦችን አይን)። ግንዱ ለተለያዩ የቤት እቃ መስሪያነት ይጠቅማል፣ ለቅርጻቅጽም እንዲሁ።
በ1968 ዓም በተዘገበ በአንድ ባህላዊ እምነት፣ «የሸረሪት በሽታ» የተባለ ቆዳ ችግር የዋንዛ [[አመድ]] በ[[ቅቤ]] ሲቀላቀል ለሕክምናው ይሆናል። በ1998 ዓም በጥላሁን ተክለሃይማኖት በተመራ ጥናት፣ በ[[ደብረ ሊባኖስ]] ዙሪያ ሰዎች ለ«ምች» ([[ትኩሳት]]) ተጠቅመውታል። በዚህ ጥናት በተሰጠው ዝግጅት፣ የዋንዛ፣ የ[[ብሳና]]፣ የ[[ነጭ ባሕር ዛፍ]] ቅጠሎች፣ እና የ[[ዳማ ከሴ]] ቅጠሎችም አገዶችም፣ ተቀላቅለው በውኃ ተፈልተው እንፋሎቱ በአፍንጫና በአፍ ይተንፈሳል።
|