ከ«ኢትዮጵያ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
ጽሑፉን በሙሉ ደመሰሰ።
Tags: Blanking blanking
No edit summary
መስመር፡ 1፦
{{መለጠፊያ:ዋቢ
|ቀን=፬ ነሐሴ ፳፻፮
}}
 
{{የሀገር መረጃ
|ስም = ኢትዮጵያ
|ሙሉ_ስም = የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
|ማኅተም_ሥዕል = Emblem of Ethiopia.svg
|ባንዲራ_ሥዕል = Flag of Ethiopia.svg
|መዝሙር = [[:dv:ޤައުމީ ސަލާމް|ወደፊት ገስግሺ ውድ እናት ኢትዮጵያ]]<br /><br><center>[[ስዕል:Gaumii salaam.ogg]]</center>
|ካርታ_ሥዕል = Ethiopia in its region.svg
|ካርታ_መግለጫ_ፅሁፍ = ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ቀለም
|ዋና_ከተማ = [[አዲስ አበባ]]
|ብሔራዊ_ቋንቋ = [[አማርኛ]] <small>ሌሎች ቋንቋዎች ክልላዊ ዕውቅና አላቸው</small>
|የመንግስት_አይነት = ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ
|የመሪዎች_ማዕረግ = [[ፕሬዝዳንት]]<br />[[ጠቅላይ ሚኒስትር]]
|የመሪዎች_ስም = ወ/ሮ [[ሳህለወርቅ ዘውዴ]]<br />ዶ/ር [[አብይ አህመድ]]
|የመሬት_ስፋት = 1,104,300
|የመሬት_ስፋት_ከዓለም = 26
|ውሀ_ከመቶ = <br>0.7
|የሕዝብ_ብዛት_ግምት_ዓመት = ፳፻ ዓ.ም.
|የሕዝብ_ብዛት_ቆጠራ_ዓመት = ፲፱፻፺፱ ዓ.ም.
|የሕዝብ_ብዛት_ግምት = 93,578,567
|የሕዝብ_ብዛት_ቆጠራ = <br>96,787,564
|የሕዝብ_ብዛት_ከዓለም = 13
|የገንዘብ_ስም = ብር
|ሰዓት_ክልል = +0
|የስልክ_መግቢያ = 251
|ከፍተኛ_ደረጃ_ከባቢ = .et
}}
 
'''ኢትዮጵያ''' ወይም በይፋ '''የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢ.ፌ.ዲ.ሪ.)''' በ[[የአፍሪካ ቀንድ|አፍሪካ ቀንድ]] የምትገኝ የረጅም ዘመን [[ታሪክ]] ያላት ሀገር ናት። በ[[አፍሪካ]] ነፃነታቸውን ጠብቀው ለመኖር ከቻሉ ሁለት [[አገሮች]] አንዷ ነች። በህዝብ ብዛት ከአፍሪካ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ስትሆን ፣ በቆዳ ስፋት ደግሞ አስረኛ ናት። [[ዋና ከተማ|ዋና ከተማ]]ዋ [[አዲስ አበባ]] ናት።
 
አብዛኛዎቹ የአፍሪካ ሀገሮች ዕድሜያቸው ከአንድ ምዕተ-ዓመት የሚያንስ ሲሆን ፣ ኢትዮጵያ ግን ከጥንት ጊዜ ጀምሮ [[ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ|በንጉሠ-ነገሥታት]] እና ንግሥተ-ነግሥታት የተመራች ሀገር ናት። የ[[ሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥት]] የአመጣጡን ዘር እስከ አስረኛው ዓመተ-ዓለም ድረስ ይቆጥራል። ኢትዮጵያ [[የሰው ልጅ]] ከጥንት ጊዜ ጀምሮ የኖረባት ቦታ እንደሆነች ብዙ የሳይንሳዊ መረጃ ተግኝቷል። በ[[የበርሊን ጉባኤ|በርሊን ጉባኤ]] በኩል የአውሮፓ ሀያላት ሀገሮች አፍሪካን ሲከፋፍሏት፣ ኢትዮጵያ ነፃነቷን ጠብቃለች። የ[[ሊግ ኦፍ ኔሽንስ|ሊግ ኦፍ ኔሽንስ (''League of Nations'')]] አባል ከነበሩት ሶስት የአፍሪካ ሀገሮች አንዷ ነበረች። ከአጭር [[የኢጣልያ ወረራ]] ጊዜ በኋላም ከ[[የተባበሩት መንግሥታት]] መሥራቾች አንዷ ናት። ከ[[ሁለተኛው የዓለም ጦርነት]] በኋላ ብዙ የአፍሪካ ሀገራት ነፃነታቸውን ሲያገኙ፣ [[ሰንደቅ አላማ|ሰንደቅ-አላማቸውን]] በኢትዮጵያ ቀለሞች ማለትም በ[[አረንጓዴ]] ፣ [[ቢጫ]] እና [[ቀይ]] ላይ ነው የመሠረቱት። አዲስ አበባ ደግሞ ለየተለያዩ በአፍሪካ ላይ ላተኮሩ አለም አቀፍ ድርጅቶች መቀመጫ ሆነች።
 
የዛሬዋ ኢትዮጵያ የትልቅ የግዛት ለውጥ ውጤት ናት። ከሰሜን ግዛቱዋ በጣም የተቀነሰ ሲሆን በደቡብ በኩል ደግሞ ተስፋፍቷል። በ [[1967|፲፱፻፷፯ (1967)]] ዓ.ም.፣ [[ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ]] ከሥልጣን ሲወርዱ፣ የእርስ በርስ ጦርነት በሀገሩ ተባባሰ። ከዚህ ጊዜ በኋላ ኢትዮጵያ በተለያዩ የመንግሥት አይነቶች ተዳድራለች። ዛሬ አዲስ አበባ [[የአፍሪካ ሕብረት]] (''African Union'') እና [[የተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚክ ኮሚሽን ለአፍሪካ]] መቀመጫ ናት። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ከአፍሪካ ኃያል ሠራዊቶች አንዱ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪቃ የእራሷ ጥንታዊ ፊደል ያላት ሀገርም ናት።
 
ኢትዮጵያ ተፈጥሮ ያደላት ሀገር ናት። ከአፍሪካ ትላልቅ ተራራዎች እንዲሁም ከዓለም ከባህር ጠለል በታች በጣም ጥልቅ ከሆኑ ቦታዎች አንዳንዶቹ ይገኙባታል። [[ሶፍ ዑመር]] ከአፍሪካ ዋሻዎች ትልቁ ሲሆን ፣ [[ዳሎል]] ከዓለም በጣም ሙቅ ቦታዎች አንዱ ነው። ወደ ሰማንኒያ የሚቆጠሩ ብሔሮችና ብሔረሰቦች ዛሬ በኢትዮጵያ ይገኛሉ። ከእነዚህም [[ኦሮሞ]]ና [[አማራ]] በብዛት ትልቆቹ ናቸው። ኢትዮጵያ በኣክሱም ሓውልት፣ ከአንድ ድንጋይ ተፈልፍለው በተሰሩ ቤተ-ክርስትያኖቹዋ እና በ[[ኦሎምፒክ]] የ[[ወርቅ]] ሜዳልያ አሸናፊ አትሌቶቹዋ ትታወቃለች። የ[[ቡና]] ፍሬ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘው በኢትዮጵያ ሲሆን ሀገሪቱዋ በቡናና [[ማር]] አምራችነት በአፍሪካ ቅድሚያ ይዛለች።
 
ኢትዮጵያ ከዓለም ሶስቱ ትላልቅ የአብርሃም ሀይማኖቶች ጋር ታሪካዊ ግንኙነት አላት። [[ክርስትና]]ን በአራተኛው ምዕተ-ዓመት ተቀብላለች። ከሕዝቡ አንድ ሁለተኛው [[ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና]] ነው። የመጀመሪያው የእስላም [[ሂጅራ]] ወደ ኢትዮጵያ ነው የተከናወነው። [[ነጋሽ]] በአፍሪካ የመጀመሪያው የእስላም መቀመጫ ናት። እስከ ፲፱፻፸ ዎቹ ድረስ ብዙ [[ቤተ እስራኤል|ቤተ-እስራኤሎች]] በኢትዮጵያ ይኖሩ ነበር። የ[[ራስ ተፈሪ እንቅስቃሴ]] ኢትዮጵያን በትልቅ ክብር ነው የሚያያት።
 
ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ከስልጣን ከወረዱ በኋላ ድህነት በኢትዮጵያ በጣም ተስፋፍቶ ነበር። ሰማኒያ አምስት ከመቶ በላይ የሚሆነው የ[[ናይል]](ኣባይ) ወንዝ ውሀ ከሀገሩ የሚመጣ ቢሆንም በ ፲፱፻፸ ዎቹ በተከሰቱ ድርቆች በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ሞተዋል። ነገር ግን ቀስ በቀስ ሀገሩዋ እያገገመች ነው። ዛሬ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአፍሪካ ውስጥ በፍጥነት ከሚያድጉት አንዱ ነው።
 
== ስያሜ ==
''ኢትዮጵያ'' የሚለው ቃል አመጣጥ በተለያዩ የታሪክ ምሁራን የተለያየ ገለፃ ሲኖረው በጣም ተአማኒነት ካገኙት አንዱ [[አይቲዮፒያ (የግሪክ ቃል)]] የሚለው ቃል ነው።
 
ኢትዮጵያ ድሮ ለውጭ አገራት '''አቢሲኒያ''' በሚል መጠሪያ ትታወቅ ነበር ፤ ይህም ስያሜ የመጣ ከ[[ሀበሻ]] ነበር።
 
'''ኢትዮጵያ''' የሚለው ስም ጥንታዊነት የሚታወቅ ከ[[ግሪክ (ቋንቋ)|ግሪክ]] ጸሐፍት ነው። ከሁሉ ቀድሞ የሆነው ግሪክ ባለቅኔ [[ሆሜር]] (፰፻ ዓክልበ. ያሕል) ይጠቅሰዋል። በግሪክ አጠቃቀም ከ[[ሳህራ በረሃ]] በስተደቡብ ላለው የአፍሪካ አህጉር ክፍል በሙሉ ሲገልጽ ፣ በተለይ ለ[[ኩሽ]] በሚነካ ትርጉሞች ይገኛል። [[ፕሊኒ]] እንደሚለው ፣ ቃሉ የመጣ [[አይቲዮፕስ]] ከተባለ ግለሠብ ነበር። እንዲሁም በኢትዮጵያ መጽሐፍት ልማድ የሀገሩ ስም የ[[ኩሽ (የካም ልጅ)|ኩሽ]] ልጅ [[ኢትዮጲስ]] ሞክሼ ነው። ሆኖም በአቅራቢያው እንደ መንግሥት ስም መጀመርያ የተመዘገበው ዘመን የ[[አክሱም]] ንጉሥ [[ኤዛና]] ዘመነ-መንግሥት ([[4ኛው ክፍለ ዘመን|፬<sup>ኛው</sup> ክፍለ ዘመን]] ዓ.ም.) ነበር።
 
አንዳንድ የኢትዮጵያ ጸሐፊ «[[ኢቅጢዮፋጊ]]» («አሣ በሎች») የሚለው ግሪክኛ ስም የ«ኢትዮጵያ» ድጋሜ ሆኖ የስያሜው ጥንታዊነትና ኗሪነት ምስክር ነው የሚል አሣብ አቅርበዋል። በዚህ አሣብ ስሙ በውነት «[[ዕንቁ]]» «[[ቶጳዝዮን]]» ከሚሉ ቃላት ጋር ዝምድና እንዳለው ባዮች ናቸው። [[መጽሐፈ ኢዮብ]] ፳፰፡፲፱ ደግሞ «የኢትዮጵያ (የኩሽ) ቶጳዝዮን» ይጠቅሳል።
 
በ[[9ኛው ክፍለ ዘመን|፱<sup>ኛው</sup> ክፍለ ዘመን]] ዓ. ም. የ[[ቢዛንታይን]] ሊቃውንት በጻፉት ሃልዮ ዘንድ ፣ «አይቲዮፒያ» የሚለው ስም የመጣ ከግሪኩ ቃላት «አይቶ» (አቃጥላለሁ) እና «ኦፕስ» (ፊት) ነበር። ይህ አስተሳሰብ እስካሁን ድረስ በምዕራብ ሊቃውንት ተቀባይነት አለው።
 
== ታሪክ ==
=== ቅድመ ታሪክ ===
ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ የሰው ልጅ ከነበረባችው ቦታዎች አንዷ መሆኗ ትታወቃለች። የሰው ፍልሰት ጥናቶች ፣ የቅሪተ አካል ጥናቶችና ሌሎች የሳይንሳዊ ዘዴዎች ይህን ያረጋግጣሉ። [[ድንቅነሽ]] የምትባለው በ[[አፋር ክልል]] ውስጥ የተገኘችው አጽም በአለም በዕድሜ ሁለተኛ ጥንታዊ ናት። ከ 3.2 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ እንደኖረች ይገመታል። ሌሎችም ታዋቂ አጽሞች በኢትዮጵያ ተገኝተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ኢትዮጵያ የክርስትና እምነት ደሴት በመሆን የቆየች ታላቅ ሀገር ናት።
 
=== የመጀመሪያዎቹ መንግስታት ===
በ ፰፻ (800) [[ዓመተ ዓለም|ዓመተ-ዓለም]] አካባቢ [[ደአማት]] የሚባል መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያና ኤርትራ ተቋቋመ። በሰሜን ኢትዮጵያ የምትገኘው [[የሀ]] የደአማት ዋና ከተማ ነበረች። በ[[የመን (አገር)|የመን]] የሚኖሩት ሳባውያን በደአማት ላይ ተፅዕኖ እንደነበራቸው የሚታመን ሲሆን ይህ ተፅዕኖ ምን ያህል እንደሆነ ግን በእርግጥ አይታወቅም። ወደ ፬፻ (400) ዓመተ-ዓለም አካባቢ የደአማት መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ በትናንሽ መንግስቶች ተተካ። ከነዚህ ትናንሽ መንግስቶች አንዱ አክሱም ሲሆን አካባቢውን እንደገና በአንድነት ለመግዛት ችሎ ነበር።
 
የአክሱማውያን ስፈን በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጠንካራ መንግሥታዊ ማኅበረሰብ ነበር። በ[[ፋርስ]] ፣ [[ሮማ]] እና [[ቻይና]] ይገኙ ከነበሩ ታላላቅ መንግሥታት በወደረኛነት የሚቆጠር ትልቅ ኅይል ነበር። በ4ኛው ምእተ-ዓመት አክሱም ወደ [[ክርስትና]] ተለወጠ። በ፮<sup>ኛው</sup> ምእት ዓመት የአክሱማውያን ግዛታዊ ቁጥጥር የዛሬዋን [[የመን (አገር)|የመን]] ግዛት ይጨምር ነበር። ግን በ፮<sup>ኛው</sup> እና በ ፰<sup>ኛው</sup> አምኣት የአክሱም ሥልጣኔ በ[[እስልምና]] መነሣት እና መስፋፋት ተዳክሞ ለውድቀት በቃ ። ተከታዩ [[የዛጔ ሥርወ-መንግሥት]] ልክ በድንገት እንደተነሳ በድንገት ሲያበቃ ፣ [[ይኵኖ አምላክ]] ሥልጣን በ [[1262|፲፪፻፷፪ (1262)]] ዓ. ም. ጨበጡ ፤ እንዲያም ሲል የ[[ሰለሞናዊው ሥርወ-መንግሥት]]ን መለሱ።
 
=== ከአውሮፓ ጋር የታደሰ ግንኙነት ===
[[ስዕል:ET Gondar asv2018-02 img03 Fasil Ghebbi.jpg|thumb|right|የንጉሠ ነገሥት ፋሲለደስ ቤተ-መንግሥት]]
በ ፲ ፭<sup>ኛው</sup> ምዕተ-ዓመት መጀመሪያ ኢትዮጵያ ከአክሱም ጊዜ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአውሮፓ ጋር ግንኙነት ጀመረች። ከ[[እንግላንድ|እንግሊዝ]] ንጉሥ [[ሄንሪ አራተኛ|ሄነሪ አራተኛ (Henry IV)]] ወደ የአቢሲኒያ ንጉሠ-ነገሥት የተላከ ደብዳቤ እስከ ዛሬ ድረስ አለ። በ[[1428 እ.ኤ.አ.]] [[አፄ ይስሐቅ]] ወደ የ[[አራጎን]] ንጉሥ [[አልፎንዞ አምስተኛ|አልፎንዞ አምስተኛ (''Alfonso V'')]] ሁለት መልክተኞች ልከው ነበር። ግን የመጀመራያው ያልተቋረጠ ግንኙነት በአፄ [[ልብነ ድንግል]] ስር ከ[[ፖርቱጋል]] ጋር ከ[[1508 እ.ኤ.አ.]] ጀምሮ ነው የተካሄደው።
 
ኢትዮጵያ በ[[አህመድ ግራኝ]] ስትጠቃ ፣ ፖርቱጋል አራት መቶ ወታደሮችና የጦር መሳሪያ በመላክ ኢትዮጵያን ረድታለች። አፄ [[ሱስንዮስ]] በፖርቱጋልና [[እስፓንያ]] ተጽዕኖ እና ተጨማሪ እርዳታ ከመፈለጋቸው የተነሳ ወደ የ[[ሮማ ካቶሊክ ክርስትና]] ተለወጡ ፤ የኢትዮጵያ ይፋ ሀይማኖትንም አደረገቱት። ይህ ውሳኔ ወደ ግዙፍ ተቃውሞና ጦርነት አመራ። በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ከሞቱ በኋላ ፣ የአፄ ሱስንዮስ ልጅ አፄ [[ፋሲለደስ]] በ [[1632 እ.ኤ.አ.]] ኢትዮጵያ ወደ አርቶዶክስ ክርስትና መመለሷን አወጁ። አውሮፓውያኖቹንም ከኢትዮጵያ አስወጡ።
 
=== ዘመነ መሳፍንት ===
[[ስዕል:ST-Theodore.jpg|thumb|left|አፄ ቴዎድሮስ በአንበሶች ተከበው]]
ከ [[1755|፲፯፻፶፭ (1755)]] እስከ [[1855|፲፰፻፶፭ (1855)]] እ. ኤ. አ. ኢትዮጵያ እንደገና ከአለም ጉዳዮች ተገላ ነበር። ይህ ጊዜ «ዘመነ-መሳፍንት» ይባላል ምክኒያቱም የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥቶች በራስ [[ሚካኬል ስሁል]] ፣ ራስ [[ወልደ ሥላሴ]] ፣ ራስ [[ጉግሳ]] እና በመሳሰሉት ቁጥጥር ስር ነበሩ። ራስ ጉግሳ በ፲፯<sup>ኛው</sup> ክፍለ ዘመን ጎንደርን በመምራታቸው የቤተ-መንግሥቱን ቋንቋ ከአማርኛ ወደ ኦሮምኛ ለውጠው ነበር።
 
የኢትዮጵያ ግለልኘነት ያበቃው ከ[[ዩናይትድ ኪንግደም|እንግሊዝ]] ጋር ግንኙነት ስትጀምር ነው። ኢትዮጵያ እንደገና የተዋሀደችው እንዲሁም የዘውዱ ስልጣን የተጠናከረው በ [[1855|፲፰፻፶፭ (1855)]] እ. ኤ. አ. በ[[አፄ ቴዎድሮስ]] ምክኒያት ነው። የሰሜን አሮሞዎችና ትግሬዎች አመፅና የግብፆች ተደጋጋሚ ድንበር መጣስ የአፄ ቴዎድሮስ ስልጣን እንዲዳከም አደረጉት። በመጨረሻም ከ[[ዩናይትድ ኪንግደም|እንግሊዝ]] ጋር በነበረው ጦርነት እስረኛ አልሆንም ብለው አፄ ቴዎድሮስ እራሳቸውን አጠፉ። በ [[1868|፲፰፻፷፰ (1868)]] እ. ኤ. አ. ኢትዮጵያና ግብፅ [[ጉራ]] በሚባለው ቦታ ተዋጉ። በአፄ [[ዮሐንስ አራተኛ]] የተመሩት የሰሜን ኢትዮጵያ ኃይሎች ድል ተቀናጁ።
 
በ [[1889|፲፰፻፹፱ (1889)]] እና በ [[1890|፲፰፻፺ (1890)]] ዎቹ እ.ኤ.አ. መጀመሪያ ፣ የሸዋ ንጉሥ ሳህለ ሥላሴ ከዚያም ዳግማዊ አፄምኒልክ በ[[ራስ ጎበና]] እርዳታ አማካኝነት ሀገሯን ወደ ደቡብና ምሥራቅ ማስፋፋት ጀመሩ። ከአህመድ ግራኝ ወረራ በኋላ በኢትዮጵያ ቁጥጥር ስር ያልነበሩ ፣ ሌሎች ደግሞ በማንኛው ጊዜ በኢትዮጵይ ቁጥጥር ስር ያልነበሩ ቦታዎች በዳግማዊ አፄ ምኒልክ አገዛዝ ጊዜ በኢትዮጵያ ስር ሆኑ። ከዚህ ጊዜ በኋላ የኢትዮጵያ ድንበር ብዙ አልተለወጠም። ከ [[1888|፲፰፻፹፰ (1888)]] እስከ [[1892|፲፰፻፺፪ (1892)]] እ. ኤ. አ. ድረስ የነበረው የሰፋ ድርቅ ከኢትዮጵያ ህዝብ በአንድ ሶስተኛ የሚገመተውን ቀጥፎአል።
 
=== የአውሮፓ ሽሚያ ለአፍሪካ ===
በ ፲፰፻፹ (1880) ዎቹ እ. ኤ. አ. የ[[አውሮፓ]] መንግሥቶች በ[[የበርሊን ጉባኤ|በርሊን ጉባኤ]] ተስማምተው አፍሪካን በቅኝ ገዢነት መከፋፈል ጀመሩ። በኢትዮጵያ እና [[ጣልያን]] መካከል የነበሩ የዚያ ዘመን ውዝግቦች ወደ [[የአድዋ ጦርነት|አድዋ ጦርነት]] በ ፲፰፻፹፰ (1888) ዓ. ም. አመሩ። በጦርነቱ የጣልያን ትልቅ ዘመናዊ ጦር በኢትዮጵያ ጦር ትልቅ ሽንፈት የደረሰበት መሆኑ ዓለምን አስደነቀ።
 
=== የግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ===
[[ስዕል:Selassie_restored.jpg|thumb|right|ግርማዊ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ]]
በ ፳<sup>ኛው</sup> ምእት ሁለተኛው ሩብ [[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]] ኢትዮጵያን ከ[[ልጅ ኢያሱ]] በኋላ መምራት ጀመሩ። ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ለ[[የአፍሪካ ሕብረት|አፍሪካ ሕብረት]] መቋቋም ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።
 
የኢትዮጵያ ነጻነት በጣልያን ወረራ ከ [[1936|፲፱፻፴፮ (1936)]] እስከ [[1941|፲፱፻፵፩ (1941)]] እ. ኤ. አ. ድረስ ቢጠቃም በጀግኖችዋ መከታ ተጠብቋል። በአዚህ ጥቃት ጊዜ ዓፄ ኃይለሥላሴ በ [[1935|፲፱፻፴፭ (1935)]] እ. ኤ. አ. በሊግ ኦፍ ኔሽንስ (League of Nations) ፊት የሚታወስ ንግግር በአማርኛ አደረጉ። ይህ ንግግር በዓለም ታዋቂ አደረጋቸው። እንዲሁም በ ፲፱፻፴፭ (1935) እ.ኤ.አ. በ [[ታይም|ታይም (''Time'')]] መጽሄት «የዓመቱ ሰው» አስባላቸው። ጣልያን ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ውስጥ መሳተፍ ስትጀምር ፣ [[ዩናይትድ ኪንግደም|እንግሊዝ]] ከኢትዮጵያዊ ተዋጊዎች ጋር ኢትዮጵያን ነጻ አወጣች። ግን እስከ [[1943|፲፱፻፵፫ (1943)]] እ. ኤ. አ. ድረስ አንዳንድ ጣልያኖች በደፈጣ ያለ ስኬት ይዋጉ ነበር። በ [[1942|፲፱፻፵፪ (1942)]] እ. ኤ. አ. ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ባርነት እንደ ተከለከለ አወጁ።
 
ዓፄ ኃይለ ሥላሴ ጀግና ሆነው ቢታዩም ፣ የ [[1973|፲፱፻፸፫ (1973)]] እ.ኤ.አ. ዓለም አቀፍ የነዳጅ ቀውስ ፣ የምግብ ዕጥረትና የድንበር ጦርነቶች ተቃውሞ አስነሱ። ከዚያም በ [[1974|፲፱፻፸፬ (1974)]] እ. ኤ. አ. በ[[ሶቪየት ሕብረት]] የተደገፈውና በ[[መንግስቱ ኃይለ ማርያም]] የተመራው [[ደርግ]] (ደርግ ማለት ኮሚቴ ማለት ነው) ዓፄ ኃይለ ሥላሴን ከስልጣን አስወረደ።
 
=== ኮምዩኒዝም ===
የተለያዩ መፈንቅለ መንግሥቶች ፣ የሰፋ ድርቀትና ስደተኞች የደርግ ሥርዓት ትልቅ ችግሮች ነበሩ። በ [[1977|፲፱፻፸፯ (1977)]] እ. ኤ. አ. [[ሶማሊያ]] [[ኦጋዴን]]ን በመውረሯ የ[[ኦጋዴን ጦርነት]] ተነሳ። በሶቪየት ሕብረት ፣ [[ኩባ]] ፣ [[ደቡብ የመን]] ፣ [[ምስራቅ ጀርመን]]ና [[ሰሜን ኮሪያ]] የመሳሪያ እርዳታ እንዲሁም ወደ ፲፭ ሺህ በሚቆጠሩ የኩባ ወታደሮች ድጋፍ አማካኝነት ደርግ ኦጋዴንን እንደገና መቆጣጠር ቻለ።
 
በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች በ[[ቀይ ሽብር]] ፣ የግዴታ ስደት ፣ ወይም ረሀብ ሞተዋል። መንግስቱ ቀይ ሽብር ያካሄደው በተቀዋሚዎች በተፈጸመው [[ነጭ ሽብር]] መልስ እንደሆነ ጠቅሷል። በ [[2006|፳፻፮ (2006)]] እ. ኤ. አ. መንግስቱ ኃይለ ማርያም በሌሉበት የሞት ቅጣት ተፈርዶባቸዋል።
 
በ ፲፱፻፹ (1980) ዎቹ መጀመሪያ የተከሰቱ ድርቀቶች ምክኒያት ስምንት ሚሊዮን የሚሆን ሕዝብ ሲራብ ፣ አንድ ሚሊዮን ደግሞ ሞተዋል። ተቃውሞ በትግራይና ኤርትራ ክልሎች ተስፋፋ። በ [[1989|፲፱፻፹፱ (1989)]] እ. ኤ. አ. [[ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ|ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ]] ከሌሎች እንቅስቃሴዎች ጋር በመቀናጀት [[የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር|የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባርን]] መሠረተ። የሶቪየት ሕብረትም ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ መቀነስ ጀመረች። የኢኮኖሚ ችግሮች ተከሰቱ ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ተዳከመ።
 
በሜይ [[1991|፲፱፻፺፩ (1991)]] እ. ኤ. አ. የኢ. ህ. አ. ዴ. ግ. ጦር ወደ አዲስ አበባ አመራ። የመንግስት ኃይሎች ምንም አይነት የውጭ እርዳታ ስላላገኙ ፣ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ.ን ጥቃቶች መቋቋም አልቻሉም። መንግስቱ ኃይለ ማርያም ወደ [[ዚምባብዌ]] ሄደው እስከ ዛሬ ድረስ በዛችው ሀገር ይኖራሉ። ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ. ፹ ፯ አባላት ያሉት የሽግግር መንግሥት መሠረተ። በጁን [[1992|፲፱፻፺፪ (1992)]] እ. ኤ. አ. የ[[ኦሮሞ ነጻነት ግንባር|ኦሮሞ ነጻነት ግንባር]] ፣ እንዲሁም በማርች [[1993|፲፱፻፺፫ (1993)]] እ. ኤ. አ. [[የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረት]] የሽግግር መንግሥቱን ለቀው ወጡ። በ [[1994|፲፱፻፺፬ (1994)]] እ. ኤ. አ. ሁለት የሕግ አውጪ ምክር ቤቶችንና የፍትሕ ስርዓትን የሚደነግግ አዲስ ሕገ መንግሥት ተፃፈ። የመጀመሪያው ምርጫ በሜይ [[1995|፲፱፻፺፭ (1995)]] እ.ኤ.አ. ተካሄደ። [[መለስ ዜናዊ|አቶ መለስ ዜናዊ]] ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሁም [[ነጋሶ ጊዳዳ|ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ]] ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ።
 
=== በቅርብ ጊዜ ===
በየተባበሩት መንግሥታት ውሳኔ ኢትዮጵያና ኤርትራ በፌደሬሽን ተዋህደው ነበር። በ ፲፱፻፺፫ (1993) እ.ኤ.አ. በተካሄደውና የተባበሩት መንግሥታት በታዘበው ሕዝበ ድምፅ ፣
 
በወቅቱ ስልጣንን በጠመንጃ አፈሙዝ የያዙትና የኤርትራን መገንጠል በሚፈልጉት በህውአትና ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ አማካይነት ለኤርትራ ህዝብ ‹ባርነት› ወይንስ ‹ነፃነት› ተብሎ እንዲመርጡ ተገደው ማንም ባርነትን የሚመርጥ የለምና ነፃነትን መረጡ ተባሎ  በረሃ ገብተው ሲታገሉለት የነበረውን አላማ ስልጣናቸውን በመጠቀም አስፈፅመው ከ ፺፱ ከመቶ በላይ የሚሆነው የኤርትራ ሕዝብና በውጭ ሀገር የነበሩ ኤርትራውያን ከኢትዮጵያ መገንጠልን መርጠዋል። በሜይ ፳፬ ፣ ፲፱፻፺፫ (1993) እ. ኤ. አ. ኤርትራ ከኢትዮጵያ ነፃነቷን አወጀች።
 
በሜይ [[1998|፲፱፻፺፰ (1998)]] እ. ኤ. አ. የድንበር ውዝግብ እስከ ጁን [[2000|፳፻ (2000)]] እ. ኤ. አ. ወደ ቀጠለው [[የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት]] አምርቶአል። ይህ ጦርነት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚን ጎድቶአል። በሜይ ፲፭ ፣ [[2005|፳፻፭ (2005)]] እ.ኤ.አ. አጠቃላይ ምርጫ ቢካሄድም ተቃዋሚዎች ማጭበርበር እንደነበረ ወንጅለዋል። በአጠቃላይ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከ ፪፻ (200) በላይ የፓርላማ መቀመጫዎችን አሸንፈዋል። ግን አንዳንድ የ[[ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ]] ፓርቲ አባሎች ከምርጫው በኋላ ከነበረው ረብሻ ጋር በተያያዘ ታስረው ነበር። በአሁኑ ጊዜ ያለው የፖለቲካ ስርአት በብሄር ላይ የተመሰረተ ፌደራላዊ ስርአት ነው፡፡
 
== መልክዓ-ምድር ==
ኢትዮጵያ በሰሜን [[ምስራቅ አፍሪካ]] ከ 3-14 ዲግሪ ሰሜን እና ከ 33-48 ዲግሪ ምሥራቅ የምትገኝ አገር ስትሆን የቆዳ ስፋቱዋም 1,127,127 ካሬ ኪ.ሜ. ነው። በሰሜን ከ[[ኤርትራ]] ፣ በምዕራብ ከ[[ሱዳን]]ና [[ደቡብ ሱዳን]] ፣ በደቡብ ከ[[ኬኒያ]] ፣ እንዲሁም በምሥራቅ ከ[[ጅቡቲ]] እና ከ[[ሶማሊያ]] ጋር ትዋሰናለች። የኢትዮጵያ አብዛኛው ግዛት በተራሮች እና አንባዎች የተሞላ ሲሆን ፣ ታላቁ የምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ እነዚህኑ ከፍተኛ ቦታዎች ከሰሜን ምሥራቅ ወደ ደቡብ ምዕራብ በመጋደም ለሁለት ይከፍላቸዋል። በስምጥ ሸለቆው ዙሪያም በረሃማ የሆኑ ዝቅተኛ ቦታዎች ይገኛሉ። ይሄን መሰሉ የ[[መልክዐ፡ምድር (ጂዎግራፊ)|መልክዓ-ምድር]] ልዩነት አገሪቷ የተለያዩ የአየር ንብረት ፣ የአፈር ፣ የዕፅዋት እና የሕዝብ አሰፋፈር ገጽታዎች እንዲኖሯት አስችሏታል። በከፍታና በመልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ የተነሣ በኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ዓይነት የአየር-፡ ንብረት ክልሎች ይገኛሉ። እነሱም፦
* ደጋ – ከፍታቸው ከባሕር ጠለል 2400 ሜትር የሚጀምር እና የሙቀት መጠናቸው ከ 16 ዲግሪ ሴ. ግ. የማይበልጥ
* ወይናደጋ – ከፍታቸው ከባሐር ጠለል ከ 1500 እስከ 2400 ሜትር ፣ ሙቀታቸውም ከ 16 ዲግሪ ሴ. ግ. እስከ 30 ዲግሪ ሴ. ግ. የሚደርስ ፣ እና
* ቆላ – ከባህር ጠለል በታች ጀምሮ እስከ 1500 ሜትር ከፍታ ያላቸው ፣ የሙቀት መጠናቸውም ከ 30 ዲግሪ ሴ. ግ. እስከ 50 ዲግሪ ሴ. ግ. የሚደርስ አካባቢዎች ናቸው።
ዋናው የዝናብ ወቅት ከሰኔ አጋማሽ እስከ መስከረም አጋማሽ ሲሆን ፣ ከሱ ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ የሚጥል የበልግ ዝናብ በየካቲት እና በመጋቢት ይከሰታል። የተቀሩት ወራት በአብዛኛው ደረቅ ናቸው።
 
== አስተዳደራዊ ክልሎች ==
ከ [[1996|፲፱፻፺፮ (1996)]] እ.ኤ.አ. በፊት ኢትዮጵያ በ ፲፬ ክልሎች ተከፍላ ነበር። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጽያ ውስጥ ፱ አስተዳደራዊ ክልሎች ይገኛሉ። አወቃቀራቸውም በህገ-መንግስቱ በተደነገገው መሰረት «በህዝብ አሰፋፈር ፤ ቋንቋ ማንነት እና ፈቃድ ላይ» ተመስርቶ ሲሆን ክልሎቹም፦
* የ[[ትግራይ ክልል]]
* የ[[አፋር ክልል]]
* የ[[አማራ ክልል]]
* የ[[ኦሮሚያ ክልል]]
* የ[[ሶማሌ ክልል]]
* የ[[ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል]]
* የ[[ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል]]
* የ[[ጋምቤላ ሕዝቦች ክልል]]
* የ[[ሀረሪ ሕዝብ ክልል]] ሲሆኑ በተጨማሪም
* [[አዲስ አበባ]] እና
* [[ድሬዳዋ]] እራሳቸውን የቻሉ የአስተዳደር አካባቢዎች ሆነው ተዋቅረዋል።
 
== ሕዝብ ==
ኢትዮጵያ ከ ፹ (80) በላይ የሚሆኑ ብሔረሰቦች የሚገኙባት «የብሄረሰቦች ሙዚየም» ልትሰኝ የቻለች ሀገር ነች። ትልልቆቹ ብሄረሰቦች ፣ የ[[አማራ]] ፣ እና [[የኦሮሞ]] የ[[ትግራይ]] እንደሁም የ[[ሶማሌ (ብሔር)|ሶማሌ]] ሲሆኑ እነዚሁ ብሄረሰቦች ከጠቅላላው የአገሪቱዋ ሕዝብ ቁጥር ክ 3/4<sup>ኛ</sup> በላይ የሚሆነውን ይይዛሉ።
በሃይማኖት በኩልም ሁለቱ ትልልቅ ሃይማኖቶች [[ክርስትና]] እና [[እስልምና]] በስፋት የሚተዋልባት አገር ናት። የክርስትና እምነት ተከታዮች ከ 55%-60 % ፣ እሰልምና ከ35% እሰከ 40% እንዲሁም የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ወደ 5%-8% የሚሆነውን ይይዛሉ።
 
== ቋንቋዎች ==
{{ዋና|የኢትዮጵያ ቋንቋዎች}}
 
በኢትዮጵያ ውስጥ ከ ፹ በላይ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩ ሲሆን በቋንቋም በኩል ከ ፹ በላይ የሚሆኑ ቋንቋዎች የሚነገሩባት ሀገር ናት። በአሁኑ ወቅት በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የሚነገሩት ቋንቋዎች [[አማርኛ]] እና [[ኦሮምኛ]] ሲሆኑ ፤ አማርኛ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ነዋሪዎች የመማሪያ ፤ የመገበያያ እንዲሁም የስራ ቋንቋ ሆኖ የቆየ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት የስራ ቋንቋ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች [[አፍሮ-ኤስያዊ ቋንቋዎች|አፍሮ-ኤስያዊ]] እና [[ናይሎ ሳህራዊ ቋንቋዎች|ናይሎ ሳህራዊ]] በሚባሉ ሁለት ዋና የቋንቋ ክፍሎች ሊካተቱ ይችላሉ። በአፍሮ-ኤስያዊ የቋንቋ ቤተሰብ ውስጥም [[ኩሻዊ]]፣ [[ኦሞአዊ]] እና [[ሴማዊ]] የሚባሉ ንዑስ ክፍሎች አሉ።
 
''ኩሻዊ'' ከሚባሉት ቋንቋዎች ዋና ዋናዎቹ [[ኦሮምኛ|አፋን ኦሮሞ]] ፣ [[ሶማልኛ]] ፣ [[አፋርኛ]] ፣ [[ሲዳምኛ]] ፣ [[ሃዲያኛ]] እና [[ከምባትኛ]] ሲሆኑ ከ''አባይ-ሰሃራዊ'' የቋንቋ ምድብ የሚካተቱት [[በርታኛ]] ፣ [[ኩናማኛ]] ፣ [[ጉሙዝኛ]] ፣ [[ሙርሲኛ]] እና የመሳሰሉት ናቸው። እንደ [[ወላይትኛ]] ፣ [[ጋሞኛ]] ፣ [[ከፋኛ]] ፣ [[ሃመርኛ]] የመሳሰሉት የ''ኦሞአዊ'' ቋንቋ ዘሮች ሲሆኑ አማርኛ ፣ [[ትግርኛ]] ፣ [[ጉራጊኛ]] ፣ [[ስልጢኛ]] ፣ [[ሀደሪኛ]]፣ [[አርጎብኛ]] እና መሰል ቋንቋዎች ከ''ሴማዊ'' ቋንቋዎች ይመደባሉ።
 
== ፊደል ==
የሴሚቲክ ምንጭ ያላቸው እንደ ትግርኛና አማርኛ ያሉት ቋንቋዎች የራሱ የሆነ የተለየ የ[[ፊደል]] ስርአት ያላቸው ሲሆን ይህም ኢትዮጵያን ከአፍሪቃ ብቸኛዋ ባለ ጥንት ፊደል ሀገር ያደርጋታል። እነኚህ የሴሚቲክ ምንጭ ያላችው ቋንቋዎች [[ግዕዝ]] የተባለ በአሁኑ ወቅት ከቤተክርስትያን ውጭ ለዕለት ተዕለት ግልጋሎት ላይ የማይውል ግንድ ዘር አላቸው።
 
በኣሁኑ ጊዜ ግዕዝ በዩኒኮድ ዕውቅና ያገኙትን የቢለን፣ ቤንች፣ ምኢን፣ ሙርሲ፣ ሱሪ፣ ትግረ፣ ትግርኛ፣ ኣገው፣ ኣውንጂ፣ ኦሮሚፋ፣ ዓማርኛ፣ ዲዚ፣ ዳውሮ፣ ጉሙዝ፣ ጉራጌ፣ ጋሞ ጎፋ እና ግዕዝ ቋንቋዎች የሚጋሯቸውን ቀለሞችና ሌሎች ያጠቃልላል። በፊደሉ ከሚጠቀሙ ቋንቋዎች መካከል ሓረሪ ኣንዱ ነው። መጽሓፍ ቅዱስ ሙሉዉን ወይም በከፊል ከ፲፭፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ በግዕዝ ቀለሞች በማተሚያ ቤቶች ከታተሙባቸው ቋንቋዎች መካከል ሃዲያ፣ ሲዳሞ፣ ከምባታ፣ ኦሮሞ፣ ወላይታ እና ጌዴኦ ይገኙበታል። (ደግሞ [[ኣበራ ሞላ]] ይዩ።)
 
በእጅ ጽሑፍና ማተሚያ ቤቶች ብቻ ይቀርብ የነበረው የግዕዝ ፊደል በ፲፱፻፹ ገደማ ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ ኣጠቃቀሙ ወደ ኮምፕዩተር ዞሯል። ከእዚያም ወዲህ ፊደሉ የዩኒኮድ የዓለም ፊደላት መደብ ውስጥ ስለገባ እያንዳንዱ ቀለም የእራሱ ስፍራ ኣለው። ([[:en:Ethiopic_(Unicode_block)]]) ይህ የኣማርኛ ውክፔድያ ድረገጽም የቀረበው በእዚሁ ፊደል ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህም ፊደሉን በእጅ ስልክ መጠቀም ተችሏል። ለፊደሉ ኣጠቃቀም ኣስፈላጊ ሆነው የተፈጠሩ ኣዳዲስ የቴክኖሎጂ ዘዴዎችም የዩናይትድ እስቴትስ የባለቤትነት መታወቂያ ወይንም ፓተንት ማግኘት ጀምረዋል። [http://pdfpiw.uspto.gov/.piw?Docid=09000957&homeurl=http%3A%2F%2Fpatft.uspto.gov%2Fnetacgi%2Fnph-Parser%3FSect1%3DPTO1%2526Sect2%3DHITOFF%2526d%3DPALL%2526p%3D1%2526u%3D%25252Fnetahtml%25252FPTO%25252Fsrchnum.htm%2526r%3D1%2526f%3DG%2526l%3D50%2526s1%3D9000957.PN.%2526OS%3DPN%2F9000957%2526RS%3DPN%2F9000957&PageNum=&Rtype=&SectionNum=&idkey=NONE&Input=View+first+page] [https://www.google.com/patents/US20090179778?dq=9,000,957]
 
== ባህል እና ሀይማኖት ==
{{ዋና|የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር}}
{| border="2" cellpadding="4" cellspacing="0" style="margin: 1em 1em 1em 0; border: 1px #aaa solid; border-collapse: collapse; font-size: 95%;" align="center"
|+<font size="+1">''የህዝብ በዓላት''</font>
|-
! style="background:#efefef;" | ቀን
! style="background:#efefef;" | የበዓሉ ሥም
! style="background:#efefef;" | የበዓሉ ሥም በእንግሊዝኛ
! style="background:#efefef;" | አስተያየት
|-
| [[መስከረም 1|መስከረም ፩]]
| [[እንቁጣጣሽ]]
|''Ethiopian New Year''
| &nbsp;
|-
| መስከረም ፲፯
| [[መስቀል]]
|''Finding of the True Cross''
| &nbsp;
|-
| ጥቅምት ፳፬
| [[ኢድ አል ፈጥር]]
|''End of Ramadan''
| ይለዋወጣል ፣ ይህ ቀን ለ ፲፱፻፺፰ ዓ. ም. ነው
|-
| ታህሳስ ፳፱
| [[ገና]]
|''Christmas''
| &nbsp;
|-
| ጥር ፪
| [[ኢድ አል አደሃ]]
|''Eid ul-Adha'' (''Feast of the Sacrifice'')
| ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ፲፱፻፺፰ ዓ. ም. ነው
|-
| ጥር ፲፩
| [[ጥምቀት]]
|''Epiphany''
| &nbsp;
|-
| የካቲት ፳፫
| [[የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል]]
|''Battle of Adowa Commemoration Day''
| &nbsp;
|-
| ሚያዚያ ፬
| [[መውሊድ]] (የ[[ነብዩ መሃመድ]] የልደት ቀን)
|''Birthday of The Prophet Muhammad''
| ይለዋወጣል ፣ ይህ ቀን ለ ፲፱፻፺፰ ዓ. ም. ነው
|-
| ሚያዚያ ፲፫
| [[ስቅለት]]
|''Good Friday'' (''Crucifixion'')
| ይለዋወጣል ፣ ይህ ቀን ለ ፲፱፻፺፰ ዓ. ም. ነው
|-
| ሚያዚያ ፲፭
| [[ትንሳዔ]] ([[ፋሲካ]])
|''Easter''
| ይለዋወጣል፣ ይህ ቀን ለ ፲፱፻፺፰ ዓ. ም. ነው
|-
| ሚያዚያ ፳፯
| የጀግኖች አርበኞች መታሰቢያ ቀን
|''Patriots' Day''
| &nbsp;
|-
| ግንቦት ፳
| [[ደርግ]] የወደቀበት ቀን
|''End of the Derg Regime''
| &nbsp;
|}
== የውጭ መያያዣዎች ==
*[http://pdfpiw.uspto.gov/.piw?Docid=09000957&homeurl=http%3A%2F%2Fpatft.uspto.gov%2Fnetacgi%2Fnph-Parser%3FSect1%3DPTO1%2526Sect2%3DHITOFF%2526d%3DPALL%2526p%3D1%2526u%3D%25252Fnetahtml%25252FPTO%25252Fsrchnum.htm%2526r%3D1%2526f%3DG%2526l%3D50%2526s1%3D9000957.PN.%2526OS%3DPN%2F9000957%2526RS%3DPN%2F9000957&PageNum=&Rtype=&SectionNum=&idkey=NONE&Input=View+first+page] Ethiopic Character Entry
*[https://patents.google.com/patent/US9733724B2/en] Phonetic Keyboards
{{commons|ኢትዮጵያ}}
{{የኢትዮጵያ_መረጃ}}
{{የኢትዮጵያ ከተሞች}}
{{በአፍሪካ ውስጥ የሚገኙ አገሮች}}
 
[[መደብ:ኢትዮጵያ| ]]