ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 375፦
፭. የኦሮምኛው የግዕዝ ፊደል ከሌሎቹ የግዕዝ ቀለሞች ጋር በዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ [http://archive.li/WIjry] ለኣለፉት ፴ ዓመታት በኮምፕዩተር ቀርቦ በኋላም በዩኒኮድ ዕውቅና ቢያገኝም [https://en.wikipedia.org/wiki/Ethiopic_(Unicode_block)] ሁሉም ባይሆኑ ኦሮሞዎች ግዕዙን እርግፍ ኣድርገው ጥለው ወደ ላቲኑ ስለዞሩ የተፈጠሩት ችግሮች ቀጥለዋል። ለምሳሌ ያህል ላቲን እራሱን የሚገልጸው የኮምፕዩተሩ ገበታ ላይ በኣሉት ቀለሞች ብቻ ኣይደለም። ፮. በእጅ የጽሕፈት መሣሪያ ዘመን ታይፕራይተር ዓማርኛንና ኦሮምኛን ለማስጻፍ ስለኣልቻለ ላቲን ብልጫ ነበረው። የዶክተሩ ግኝት ለእውሸቱ (የፈጠራ) የታይፕራይተር የኣማርኛ ነገሮችና ለትክክለኛዎቹ የማተሚያ ቤቶች ፊደላት ኣጠቃቀሞች እጅግ ትልቅ ፈውስ (Breakthrough) ነበር። የታይፕራይተር ፊደል ለታይፕራይተር ሲባል የተሠራ በፍፁም ትክክለኛ በኣለመሆኑና ለብዙ ምዕት ዓመታትም በእጅ ስንጽፈው የነበረው ከኣለመሆኑም ሌላ የማተሚያ ቤት ፊደላችንም ስለኣልሆነ ከቁርጥራጮች የሚሠራውን ብጥስጥስ ዶ/ር ኣበራ እውሸት ፊደል ይሉታል። ስለ ታይፕራይተሩ ድክመት ዶክተሩ እ.ኤ.ኣ. በ1991 [http://trigonal.ncat.edu/AAU-Network/news/EJSciTech/abera2.html] [https://www.facebook.com/notes/geezedit/advances-made-by-ethiopians-in-the-computer-technology-1991/403555123037729/] ስለኣቀረቡ መሣሪያው ወደ ቁቤ ለመዞር ምክንያት መሆን ኣልነበረበትም። ከእዚያም ወዲህ በኮምፕዩተር የኦሮምኛው የግዕዝ ፊደል በዶክተሩ መከተብ መቻልና የተጠቃሚዎች መኖር ግንዛቤ ውስጥ ሳይገቡ ብዙ ዓመታት ባክነዋል። ቴክኖሎጂ የችግር መፍቻ እንጂ ከችግር መሸሽያ ኣይደለም። ፯. ቁቤ በላቲን ዋየሎች ከሚጠቀምባቸው በተሻለ ኣፋን ኦሮሞ በግዕዙ ሊጠቀም ይችላል። ኦሮምኛን በፊደል ለመክተብ ከላቲኑ ቁቤ የግዕዝ ፊደል ይጠቅማል። [https://www.youtube.com/watch?v=I97bJbKbW6w] [http://www.ethiomedia.com/1000bits/geez-for-qubee.html] ፰. መጽሓፍ ቅዱስ በከፊል እ.ኤ.ኣ. በ1841 በኦሮሞ ቋንቋ በግዕዝ ፊደል ተጽፏል። [http://www.worldscriptures.org/pages/oromocentral.html] [http://www.worldscriptures.org/pages/boranaoromo.html] እንዲሁም እ.ኤ.ኣ. በ1875 የኦሮሞ ሓዲስ ኪዳን በግዕዝ ፊደል ታትሟል። [http://www.worldscriptures.org/pages/oromoeastern.html] [https://web.archive.org/web/20160405073858/http://www.worldscriptures.org/pages/oromowestern.html] [https://web.archive.org/web/20160904072134/http://www.worldscriptures.org/pages/oromoeastern.html]
 
፱. በልሳነ ግእዝና በኣፋን ኦሮሞ (ግእዚፊ ኣፋን ኦሮሞቲን - Giiiziifi Afaan Oromootiin) የተዘጋጀው [[መጽሓፈ ቅዳሴ]] - ክታባክታበ ቅዳሴ - Kitaaba Qiddaasee መጋቢት 10 ቀን 2008 ዓ.ም. በኢሊሌ ሆቴል ተመርቋል። የትርጐማና የኣርትኦት ሥራው 10 ዓመታት የወሰደው ባለ ሦስት ዓምዱ ክታበ ቅዳሴ፦ የመጀመርያው ረድፍ በግእዝ ቋንቋ፣ ሁለተኛው ረድፍ በኦሮምኛ ሆኖ በግእዝ ፊደል፣ ሦስተኛው ረድፍ በኦሮምኛ ሆኖ በቁቤ ፊደል ተጽፏል ይላል ሪፖርተር ጋዜጣ። [http://andadirgen.blogspot.com/2016/03/blog-post_27.html] ይህ የግዕዝ ፊደል ኦሮምኛን ኣይጽፍም ለሚሉት ማፈሪያ ነው። ፲. መጽሓፍ ቅዱስ ሙሉዉን ወይም በከፊል ከ፲፭፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ በግዕዝ ቀለሞች በማተሚያ ቤቶች ከታተሙባቸው ቋንቋዎች መካከል የግዕዝ ቋንቋ ([[ግዕዝኛ]])፣ [[ዓማርኛ]]፣ [[ትግርኛ]]፣ [[ኦሮምኛ]] [https://web.archive.org/web/20160904072134/http://www.worldscriptures.org/pages/oromoeastern.html] [https://web.archive.org/web/20131016202436/http://www.worldscriptures.org/pages/oromocentral.html] [https://web.archive.org/web/20160405073858/http://www.worldscriptures.org/pages/oromowestern.html] ፣ [[ሃዲያ]]፣ [[ሲዳሞ]]፣ [[ከንባታ]]፣ [[ወላይታ]]ና [[ጌዴኦ]] ይገኙበታል። [http://web.archive.org/web/20050206125215/http://www.worldscriptures.org:80/pages/sidamo.html] ስለዚህ ለዓመታት በማተሚያ ቤቶች የግዕዝ ፊደላት ሲከተብ የነበረው ኦሮምኛ ኮምፕዩተራይዝድ ሆኖ ዛሬ ሥራ ላይ እየዋለ ግዕዝ ኦሮምኛን ኣይጽፍም ማለት ሳይንስ ኣይደለም። ፲፩. በኣነሰ የኆኄያት ግድፈቶች (Spelling / እስፔሊንግ) እና ስፍራዎች (Spaces) ማስከተብ ብልጫዎች የነበረው የግዕዝ ፊደል በዶ/ር ኣበራ ግኝት የተነሳ የግዕዝ ፊደል ሓሳብን በኣነሰ ጊዜ (Time)፣ መርገጫዎች (Keystrokes) እና ገበታዎች (Keyboards) በኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች በማስከተብ ብልጫዎቹ ወደ ኣምስት ዓይነቶች ከፍ ብለዋል። ለምሳሌ ያህል “ዘ ኲክ ብራውን ፎክስ ጃምፕስ ኦቨር ዘ ሌይዚ ዶግ።” የሚለውን ዓረፍተ ነገር ላቲን በ36 ቀለሞችና በቁቤ በ45 ቀለሞች ከመክተብ ይልቅ በግዕዝ ፊደል በ24 ቀለሞች መክተብ የተሻለ ነው። ፲፪. የቁቤ ሥርዓት እ.ኤ.ኣ. በ1992 ገደማ የተመሠረተው ኣንዱ ቀለም ኣንድን ድምጽ በመወከል ነው ተብሏል። የላቲንም ሆነ የቁቤ ቀለሞች ኣንድን ድምፅ በኣንድ ቀለም ከሚወክለው የግዕዝ ፊደል ጋር የመወዳደር ችሎታ የላቸውም። ላቲን ኣንድኣንድ ድምጾችን የሚከትበው በሁለት ቀለሞች ስለሆነ ሁሉም ቀለሞች ለየብቻቸው ኣንድ ድምጽ እንዲወክሉ እንኳን ተደርጎ መጠቀም ኣይቻልም። ለምሳሌ ያህል “d” እና “h” የ“ዽ” እስፔሊንግ ስለሆኑ “ዲ” እና “ኤች”ን በሁለት ቀለምነት ጎን ለጎን ኣስቀምጦ በ“d” እና “h” ድምጽ ሰጪነት መጠቀም ኣይቻልም። ይህ ምሳሌ የሚያሳየው ቁቤ የተመሠረተው በጥቂት የኦሮሞ ምሁራን ማምታታትም ላይ መመርኰዙን ነው። ሌላ ምሳሌ ግዕዝ ማላልያና ማጥበቂያ (Long Vowels / Germination) የለውም የሚባለው ነው።
[http://samsondoya.blogspot.com/2013/07/open-response-to-yilikal-getnet.html?m=1] ለግዕዝ ዋየል ስለማያስፈልገውና ስለሌለው የሚያላላው / የሚያጠብቀው ዋየል ስለሌለው ኣንድ ቀለም የሚበቃውን የግዕዝ ማጥበቂያ ትቶ ለማጥበቅ ሲባል ወደ ኣሥር የላቲን ዋየሎች መዞር ኣያታርፍም። ለላቲን የሚያስፈልጉትን ረዣዥም ዋየሎች ግዕዝ ስለሌለው ኦሮምኛን በላቲን ለመክተብ መረጥን ለሚሉት ሰበቡ ሳይንሳዊ ስለኣልሆነ ሊታሰብበት ይገባል ይላሉ ዶክተር ኣበራ። የግዕዝ ፊደል በብዛቱ እየተወቀሰ ከእዚያ በበዙ መተካት መሞከር ትክክል አይደለም። ቁቤ የሚጠብቁ የላቲን ዋየሎችንና አንዚራን (Accents) ኣልተጠቀመም። የተለያዩ ምክንያቶች በማቅረብ የግዕዝ ፊደል ኦሮምኛን ኣይጽፍም የኣሉትን እንደተሳሳቱ ሳይጠቅሱ ኣሁንም መጥቀስ ስለጉዳዩ ኣሁንም የሚጽፉት ጥቂት ምሁራን እራሳቸውን ማረም እንዳልቻሉ ያሳያል። [https://advocacy4oromia.org/2013/10/05/the-use-of-latin-script-for-afan-oromo-writing-is-based-on-scientific-evidence/] [http://web.archive.org/web/20060516083508/http://www.ethiopic.com/ethiopic_computerization.htm] ወደ ላቲን የተዞረው ያለበቂ ጥናትና ሕዝቡ ሳያውቅና ሳይመርጥ በእውሸት ሕዝብ መረጠው ተብሎ ነው።