ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
መስመር፡ 375፦
፭. የኦሮምኛው የግዕዝ ፊደል ከሌሎቹ የግዕዝ ቀለሞች ጋር በዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ [http://archive.li/WIjry] ለኣለፉት ፴ ዓመታት በኮምፕዩተር ቀርቦ በኋላም በዩኒኮድ ዕውቅና ቢያገኝም [https://en.wikipedia.org/wiki/Ethiopic_(Unicode_block)] ሁሉም ባይሆኑ ኦሮሞዎች ግዕዙን እርግፍ ኣድርገው ጥለው ወደ ላቲኑ ስለዞሩ የተፈጠሩት ችግሮች ቀጥለዋል። ለምሳሌ ያህል ላቲን እራሱን የሚገልጸው የኮምፕዩተሩ ገበታ ላይ በኣሉት ቀለሞች ብቻ ኣይደለም። ፮. በእጅ የጽሕፈት መሣሪያ ዘመን ታይፕራይተር ዓማርኛንና ኦሮምኛን ለማስጻፍ ስለኣልቻለ ላቲን ብልጫ ነበረው። የዶክተሩ ግኝት ለእውሸቱ (የፈጠራ) የታይፕራይተር የኣማርኛ ነገሮችና ለትክክለኛዎቹ የማተሚያ ቤቶች ፊደላት ኣጠቃቀሞች እጅግ ትልቅ ፈውስ (Breakthrough) ነበር። የታይፕራይተር ፊደል ለታይፕራይተር ሲባል የተሠራ በፍፁም ትክክለኛ በኣለመሆኑና ለብዙ ምዕት ዓመታትም በእጅ ስንጽፈው የነበረው ከኣለመሆኑም ሌላ የማተሚያ ቤት ፊደላችንም ስለኣልሆነ ከቁርጥራጮች የሚሠራውን ብጥስጥስ ዶ/ር ኣበራ እውሸት ፊደል ይሉታል። ስለ ታይፕራይተሩ ድክመት ዶክተሩ እ.ኤ.ኣ. በ1991 [http://trigonal.ncat.edu/AAU-Network/news/EJSciTech/abera2.html] [https://www.facebook.com/notes/geezedit/advances-made-by-ethiopians-in-the-computer-technology-1991/403555123037729/] ስለኣቀረቡ መሣሪያው ወደ ቁቤ ለመዞር ምክንያት መሆን ኣልነበረበትም። ከእዚያም ወዲህ በኮምፕዩተር የኦሮምኛው የግዕዝ ፊደል በዶክተሩ መከተብ መቻልና የተጠቃሚዎች መኖር ግንዛቤ ውስጥ ሳይገቡ ብዙ ዓመታት ባክነዋል። ቴክኖሎጂ የችግር መፍቻ እንጂ ከችግር መሸሽያ ኣይደለም። ፯. ቁቤ በላቲን ዋየሎች ከሚጠቀምባቸው በተሻለ ኣፋን ኦሮሞ በግዕዙ ሊጠቀም ይችላል። ኦሮምኛን በፊደል ለመክተብ ከላቲኑ ቁቤ የግዕዝ ፊደል ይጠቅማል። [https://www.youtube.com/watch?v=I97bJbKbW6w] [http://www.ethiomedia.com/1000bits/geez-for-qubee.html] ፰. መጽሓፍ ቅዱስ በከፊል እ.ኤ.ኣ. በ1841 በኦሮሞ ቋንቋ በግዕዝ ፊደል ተጽፏል። [http://www.worldscriptures.org/pages/oromocentral.html] [http://www.worldscriptures.org/pages/boranaoromo.html] እንዲሁም እ.ኤ.ኣ. በ1875 የኦሮሞ ሓዲስ ኪዳን በግዕዝ ፊደል ታትሟል። [http://www.worldscriptures.org/pages/oromoeastern.html] [https://web.archive.org/web/20160405073858/http://www.worldscriptures.org/pages/oromowestern.html] [https://web.archive.org/web/20160904072134/http://www.worldscriptures.org/pages/oromoeastern.html]
፱. በልሳነ ግእዝና በኣፋን ኦሮሞ (ግእዚፊ ኣፋን ኦሮሞቲን - Giiiziifi Afaan Oromootiin) የተዘጋጀው [[መጽሓፈ ቅዳሴ]] -
[http://samsondoya.blogspot.com/2013/07/open-response-to-yilikal-getnet.html?m=1] ለግዕዝ ዋየል ስለማያስፈልገውና ስለሌለው የሚያላላው / የሚያጠብቀው ዋየል ስለሌለው ኣንድ ቀለም የሚበቃውን የግዕዝ ማጥበቂያ ትቶ ለማጥበቅ ሲባል ወደ ኣሥር የላቲን ዋየሎች መዞር ኣያታርፍም። ለላቲን የሚያስፈልጉትን ረዣዥም ዋየሎች ግዕዝ ስለሌለው ኦሮምኛን በላቲን ለመክተብ መረጥን ለሚሉት ሰበቡ ሳይንሳዊ ስለኣልሆነ ሊታሰብበት ይገባል ይላሉ ዶክተር ኣበራ። የግዕዝ ፊደል በብዛቱ እየተወቀሰ ከእዚያ በበዙ መተካት መሞከር ትክክል አይደለም። ቁቤ የሚጠብቁ የላቲን ዋየሎችንና አንዚራን (Accents) ኣልተጠቀመም። የተለያዩ ምክንያቶች በማቅረብ የግዕዝ ፊደል ኦሮምኛን ኣይጽፍም የኣሉትን እንደተሳሳቱ ሳይጠቅሱ ኣሁንም መጥቀስ ስለጉዳዩ ኣሁንም የሚጽፉት ጥቂት ምሁራን እራሳቸውን ማረም እንዳልቻሉ ያሳያል። [https://advocacy4oromia.org/2013/10/05/the-use-of-latin-script-for-afan-oromo-writing-is-based-on-scientific-evidence/] [http://web.archive.org/web/20060516083508/http://www.ethiopic.com/ethiopic_computerization.htm] ወደ ላቲን የተዞረው ያለበቂ ጥናትና ሕዝቡ ሳያውቅና ሳይመርጥ በእውሸት ሕዝብ መረጠው ተብሎ ነው።
|