ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 381፦
ነው ተብሎ በቀረበበት ጊዜ እየኣንድኣንዱ የኦሮምኛ የግዕዝ ቀለም በኮምፕዩተር በሁለት መርገጫዎች በዶክተሩ እየተከተበ ነበር። ምንም እንኳን ግዕዝ እንከን የማይወጣለት ፊደል ነው ማለት ባይቻልም ለኣንድ ድምጽ ኣንድ ቀለም ለመመደብና ኣንድን ቀለም ለኣንድ ድምጽ ለመመደብ የተፈጠረ ነው ማለት ይቻላል። ፲፬. ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን ዓማርኛ የማጥበቂያ ምልክት የለውም የሚሏቸውን ስሕተቶች ቀጥለውበታል። ዓማርኛ መጥበቅ የኣለበትን ቃል ከማይጠብቀው የሚለይበት ሁለት ዘዴዎች ኣሉት። ከእነዚህ ኣንዱ ከሚጠብቀው ቀለም ኣናት በላይ ኣንድ ነጥብ መክተብ ሲሆን ምሳሌውም በ፲፮፻፺ ዓ.ም. ታትሟል። ለምሳሌ ያህል “ላላ‘” እና “አላላ‘” ገጽ 1 እና “መነ‘ሣት” ገጽ 50 ላይ ቀርበዋል። [https://books.google.com/books?id=akBMAAAAcAAJ&printsec=frontcover#v=onepage&q&f=false] ይኸንንም ኣጠቃቀም [[ሓዲስ ዓለማየሁ]] [https://am.wikipedia.org/wiki/%E1%88%80%E1%8B%B2%E1%88%B5_%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9B%E1%8B%A8%E1%88%81] በ“ፍቅር እስከ መቃብር” መጽሓፋቸው ኣስፋፍተውታል። በኣዲስ ቅርጽ ለኮምፕዩተር እንዲስማማ መጥበቅ ከኣለበት ቀለም ኋላም እንዲከተብ ተደርጎ ማጥበቂያና ማላልያ በዶክተሩ ፓተንትም ውስጥ ኣ.ኤ.ኣ. በ2009 ተጠቅሰዋል። [http://www.google.com/patents/US20090179778] ፲፭. የቁቤ ዋየሎች “ኤ”፣ “ኢ”፣ “ኣይ”፣ “ኦ” እና “ዩ” (“a”፣ “e”፣ “i”፣ “o” እና “u”) ስለሆኑ በቁቤ “ክታበ”ን ከ“ኪታባ” የመለየትና ማጥበቅ ችግሮች ኣሉት። ይህ በኣዲስ ፊደልነት የቀረበውንም በብዛት ከግዕዝ ፊደል የበለጠውንም [https://en.wikipedia.org/wiki/Bakri_Sapalo] ይመለከታል። ግዕዝ ሰባት እንዚራን ሲኖረው ኦሮምኛ 10 ያስፈልጉታል የተባለው ትክክል ከኣለመሆኑም ሌላ ቍጥሩን መጨመርም ስለኣላዋጣም ኣልቀጠለም። ትክክለኛው የግዕዝ ኣጻጻፍ “ኣፋን” እንጂ “አፋን” ኣይደለም። ፲፮. ይህ ግዕዝና ኦሮሚፋ ሳይንሳዊ ጽሑፍ ስለ ፊደላቱ እንጂ ቋንቋዎቹን ኣይመለከትም። የኦሮሞ ቋንቋችን መዳከም ስለሌለበት ስለ ፊደል ስንወያይ ሰለ ቋንቋና ሰለኣልፈጠርናቸው ኦሮሞነት መቀላቀል ሳይንስ ኣይደለም።
 
፲፯. እነ “ሸ”፣ “ቸ”፣ “ኘ”፣ “ዸ”፣ “ጠ”፣ “ጨ”፣ “ጰ”፣ እንዚራኖቹንና ሌሎች ቀለሞች የኣሉትን ለኦሮምኛ የሚያስፈልጉትን ቀለሞች ትቶ እነዚህን ወደ የሌሉት የላቲን ፊደል መዞር ሳይንስ ኣይደለም። [http://samsondoya.blogspot.com/2013/07/open-response-to-yilikal-getnet.html?m=1] ፲፰. የኦሮምኛ ድምጾችንና እርባታዎችን የሚወክል የፊደል ገበታ (ከኣማርኛ ታይፕራይተር፣ [[ዓረብኛ]]ና [[ላቲን]]) ለጊዜው የተሻለው ላቲን ነው በማለት በስሕተት የቁቤ ኣጻጻፍ ሥራ ላይ ዋለ። ይህ ለዓማርኛው በኣለመደረጉ ዶክተሩ በመፍትሔው የደረሱለት ለኣፋን ኦሮሞ ጭምር ነው። ምክንያቱም ዓማርኛና ኣፋን ኦሮሞ በትክክለኛው የግዕዝ ፊደል ለብዙ ምዕት ዓመታት ተጠቅመዋል። [http://archive.is/LWaLI] የጄምስ ብሩስና ሌሎች መረጃዎችም ኣሉ። ስለዚህ ዓማርኛውንም ሆነ ሌሎችን ቋንቋዎቻችን ለማይጽፈው የዓማርኛ ታይፕራይተር ሲባል ፊደሉን የተዉት ቋንቋዎች በኣንድኣንድ ተናጋሪዎች ስሕተት እንጂ በግዕዝ ፊደል ሲጠቀሙ በነበሩ ኢትዮጵያውያን ስሕተት ኣልነበረም። ፲፱. በዶክተሩ ግኝቶች ከ“አ” እና “ኸ” መርገጫዎች ፲፬ የግዕዝ ቀለሞች እየተከተቡ ናቸው። [http://www.ethiomedia.com/1011issues/first_ethiopic_patent.pdf] [http://www.google.com/patents/US9733724] ፳. [[ቁቤ]] በ“a”፣ “e”፣ “i”፣ “o” እና “u” በተጠቀመው ዓይነት በ“ኣ”፣ “ኤ”፣ “ኢ”፣ “ኦ” እና “ኡ” የግዕዝ ቀለሞች መጠቀም ይችል ነበር። ኣንድኣንድ ኦሮሞዎች “ቢራ” በላቲን ኦሮሚፋ "biirraa" ተብሎ የሚጻፈው ግዕዝ ስለማይችለውም ነው ይላሉ። በ“biirraa” ምትክ “ብኢኢርርኣኣ” ተብሎ በግዕዝ ፊደል መጻፍ ይቻላል። ስለዚህ ቁቤ የተመሠረተው ሳይንሳዊ ጥቅም ላይ ኣይደለም። “ቢ” እና “ራ” ቀለሞችን ዓማርኛ በኣራት ዓይነቶች ማለትም “ቢራ”፣ “ቢ'ራ”፣ “ቢራ'” እና “ቢ'ራ'” መጠቀም ይችላል። “ብኢርኣ” ወይም “ቢርራ”ም ኣለ። ለምሳሌ ያህል “ለቅቆ” የሚለውን ቃል “ለቅቆ” ወይም “ለቆ'” ዓይነቶች መክተብና ማጥበቂያዎች መጨመርም ይቻላል። ቁቤ ዋየሎችን ከመደራረብ በ“ዓ”፣ “ዔ”፣ “ዒ”፣ “ዖ” እና “ዑ” የግዕዝ ቀለሞች ኣጠቃቀም ምሳሌዎች ጊዜ፣ ሥፍራና ጉልበት መቆጠብ ይችል ነበር።
 
፳፩. ኣንድኣንድ የኦሮሞ ምሁራን ግዕዝ የኦሮምኛ ቃላትን ኣይጽፍም በማለቱ በኣለማወቅ በስሕተቱ ገፍተውበታል። ጎዸቱ፣ ቶኮፋዸ፣ ዹፌ፣ ዹጉማ፣ ጀዺ፣ ዻባ፣ ዻራርቱ፣ ባዻዻ፣ ዻዻ፣ ጄዼ፣ ዼራ፣ ዽባፍ፣ ዽባ፣ ነንዾከዼስ ምሳሌዎች ናቸው። ፳፪. ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን “ዻ” የግዕዝ ኦሮምኛ ቀለም በኣንድ ቀለም በሁለት መርገጫዎች ከመክተብ ይልቅ “dha” በማለት በሦስት ቀለሞችና በሦስት መርገጫዎች በኦሮሚፋ መክተብ የተሻለ ሳይንስ ይመስላቸዋል። ኣንድኣንድ የግዕዝ ቀለሞችን በላቲን ለመለየት ሦስትና ከሦስት በላይ ቀለሞችን መደርደር ያስፈልጋል። ግዕዝ ለኣዳዲስ ድምጾች ፊደል ሲፈጥር ቁቤ ለኣለው ፊደል ሌላ ድምጽና እስፔሊንግ በመጨመር መሻሻል ስለሚፈልግ ችግሩን ያባብሳል። ግዕዝን በላቲን እስፔሊንግ ለመጻፍ የሞከሩትም ጥቂቶቹን እስከኣሁን የኣዋጣቸው የሕዝቡ ስለቴክኖሎጂው በሚገ'ባ ኣለመረዳት ነው። ፳፫. በሚገባ ሳይታሰብበት የግዕዝ ቀለሞች በላጭነትና ጥቅሞች ሳይገለጹ ታልፈዋል። ምሳሌ፦ ግዕዝ ችግር የለውም ማለት ሳይሆን የላቲን ቃላት እስፔሊንግ ዕድሜ ልክ ቢማሩትም ማስታወስ ኣይቻልም። በእዚህ ላይ “ኦሮሞ” የሚለው ቃል እስፔሊንግ በላቲን “Oromo” በኦሮሚፋ የኣለ በቂ ምክንያት “Oromoo” ነው። [http://www.ethiomedia.com/1000bits/testing-the-power-of-geez.pdf] [http://www.unicode.org/charts/PDF/U1200.pdf] የቁቤ ላቲንና የላቲንን እንግሊዝኛ ተደራራቢ እስፔሊንግ ማስታወስ ኣስቸጋሪነት የተነሳ ትክክለኛዎቹን ማስተማርና ማስታወስ ሳያስቸግር ኣይቀርም። ግዕዝ ኣዳዲስ ቀለሞችን እየፈጠረ ሲያድግ ቁቤ በኣሉት የላቲን ቀለሞች ላይ እስፔሊንግ መጨመር ስለኣለበት ለሁሉም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች እየጠቀመ ማደጉ ኣጠራጣሪ ነው። ስለዚህ ቁቤ የኣናሳ ተጠቃሚዎች በመሆን ኦሮሚፋን፣ ኦሮሞውንና ኢትዮጵያን ሊያቈረቍዝ ይችላል። ፳፬. በኣጠቃቀም የላቲን ፊደል ከግዕዝ ሳድሳን ቀለሞች ጋር ኣንድ ዓይነት ነው። ግዕዝ እንዚራኑን በኣንድኣንድ ቀለሞች ሲወክል ላቲን ዋየሎቹን ሳድሳኑ ጎን ማስከተብ ስለኣለበት ከሰባት ጊዜ በላይ እጥፍ ስፍራዎችን ያስባክናል። ይኸንን የግዕዝ ምሳሌ የ“ገ” 11 እንዚራን በላቲን ጠብቆና ሳይጠብቅ በመክተብ ልዩነቱን መመልከት ይቻላል።