ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 406፦
፲፫. ኣንድኣንድ ዓማርኛ ፀሓፊዎች በነጠላ ሰረዝ ምትክ የላቲኑን ኮማ (Comma) እንዲሁም በድርብ ሰረዝ ምትክ የላቲኑን ሰሚ ኮለን (Semi-colon) መጠቀም ስለጀመሩ ዶክተሩ እየተቃወሙ ናቸው። ፲፬. ኣንድኣንድ ዓማርኛ ፀሓፊዎች መጽሓፎች ሲያሳትሙ ገጾቹን ለየብቻቸው እያተሙ ይጠርዛሉ። የመጽሓፍና መጽሔት ገጾች ሲታጠፉ ቍጥሮቹና ርዕሶቹ መሳሳም ይገባቸዋል። ለምሳሌ ያህል ገጽ ኣንድ ከግራ ግርጌ ማዕዘን ከሆነ ገጽ ሁለት ከቀኝ ግርጌ ማዕዘን ላይ መሆን ይኖርበታል። ፲፭. ኣንድኣንድ ምሁራን ለዓማርኛ ቃለ ምልልስ ሲቀርቡ በዓማርኛ መናገር እንዳለባቸው ኣስቀድሞ ማስጠንቀቅ ያስፈልጋል። እንግሊዝኛ እየቀላቀሉ የሚያስቸግሩትን በማረም የኣሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ጥሩ ሥራ ይዟል። ፲፮. ኣንድኣንድ ኢትዮጵያውያን ዓማርኛውን ኣራት ነጥብ በሌለው ከመጻፍ እንዲቆጠቡና ኣራት ነጥብ በሌለውም መጻፊያ እየጻፉ ጊዜያቸውን ከማባከን ቢቆጠቡ ይጠቅማል።
 
፲፯. ኣንድኣንድ ፀሓፊዎች ሞክሼዎች የሚሏቸውን ቀለሞች በሌሏቸው ዓማርኛውን እየጻፉ ችግሮች እየፈጠሩ ናቸው። ለምሳሌ ያህል “መሳሳት"ና “መሣሣት" ወይም “ዓለማቀፍ"ና “ኣለማቀፍ" ኣንድ ኣይደሉም። ፲፰. ኣንድ የግዕዝ ፊደል በሁለት መርገጫዎች እንደተከተበ ከዶክተሩ ፈጠራ ጋር ከነማስረጃዎቹ ከቀረቡ ፴ ዓመታት ኣልፈዋል። ማንኛውንም የግዕዝ ፊደል ዛሬ በሦስትና ከእዚያ በላይ መርገጫዎች መክተብ ከተማረ ሕዝብ ኣይጠበቅም። ፲፰. ኣንድ የግዕዝ ፊደል በሁለት መርገጫዎች እንደተከተበ ከዶክተሩ ፈጠራ ጋር ከነማስረጃዎቹ ከቀረቡ ፴ ዓመታት ኣልፈዋል። ማንኛውንም የግዕዝ ፊደል ዛሬ በሦስትና ከእዚያ በላይ መርገጫዎች መክተብ ከተማረ ሕዝብ ኣይጠበቅም።
 
===የግዕዝ ቁምፊዎች===