ከ«ኣበራ ሞላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 416፦
፭. ኣንድ በግዕዝ ዩኒኮድ ቁምፊ የሚጠቀም ደራሲ ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች መክተብ መቻሉን ማጣራት የደራሲ ሥራ ነው። ምክንያቱም ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው የማተሚያ ቤቶቹን ኃላፊነት ለደራሲዎች ስለሰጡ ኣዲሱን ቴክኖሎጂ መማር ኣስፈላጊ ስለሆነ ነው። ፮. ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ ዶክተሩ በመደበኛነት (Standard) የተጠቀሙት የኢትዮጵያ ቍጥር ፩ ፊደል ነው። እ.ኤ.ኣ. በ1988 በዶክተሩ ከፖስትእስክሪፕት (Postscript) ፊደላቸው የተሠራ የመጀመሪያው ትሩታይፕ (TrueType) የግዕዝ ፊደልና ፊደላቸው ነው። ይህ እነ ብርሃንና ሰላምና የመሰሉ የኢትዮጵያ ማተሚያ ቤቶች ሲጠቀሙበት የነበረው ቁምፊ ወደ ታይምስ ሮማን (Times Roman) የእንግሊዝኛ ቁምፊ የቀረበና ተመሳሳይ ቢሆንም ከላቲኑ ጋር ሲወዳደር የግዕዝ ፊደል ተለቅና ደመቅ የኣለ ነው። ኣብዛኛዎቹ የዓማርኛና እንግሊዝኛ መጽሓፍት ሲጻፉ የነበሩት በእነዚህ ቁምፊዎች ነበር። ይህ የግዕዝ ቁምፊ መልክ ወደጎን ቀጠን ብሎ ወደታች የወፈረ ነው። በማተሚያ ቤቶቹና ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ ሲታተሙ የነበሩት መጽሓፎች የፊደል መጠን (Points) ከ10 እስከ 12 ነበር። ፰. ኣንድ የግዕዝ ቁምፊ ቢያንስ ከኣንድ ተመጣጣኝ የእንግሊዝኛ ቁምፊ ጋር መቅረብ ይኖርበታል።
 
፱. ኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች ላይ በቀላሉ ማየት እንዲቻል የሚቀርቡ ጽሑፎች ደቦልቦል በኣሉ ቁምፊዎች ነው። እነዚህን ለመጽሓፎችና ለመሳሰሉት መጠቀም ኣስፈላጊ ኣይደለም። ፲. ኣንዳኣንድ ሰዎች ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ማድረግ ፊደሉን መሥራትና ማቅረብ ይመስላቸዋል። ይህ ከኣለማወቅ የመጣ ስሕተት ነው። በፓተንት የሚጠበቀው ኣዲስ የሆነውና ፊደሉን በኮምፕዩተር መጠቀም የኣስቻላውን ዘዴ ነው እንጂ ከዘዴው ጋር ለሚቀርቡት ፊደላት ኣይደለም። ፲፩. ኣንዳኣንድ ሰዎች ግዕዝን ኣሜሪካ ፓተንት ማድረግ ፓተንቱን ወይም ፊደሉን ለኣሜሪካ መስጠት ይመስላቸዋል። ይህ ከኣለማወቅ የመጣ የፈጠራ ወሬ ነው። ፲፪. ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው ከትክክለኛው ቁምፊ ጋር ዶክተሩ ከኣቀረቡ በኋላ ከአማርኛው ቅጥልጥል ፊደል እስከኣልተሟሉና የተሳሳቱ ቀለሞች የኣሉዋቸውን ቁምፊዎች በነፃና በሽያጭ የሚያቀርቡ ኣሉ። ይኸንን መረዳትና ማስተዋል የተጠቃሚው ኃላፊነት ሲሆን ኣንባቢው ስሕተቶችን እያየ ዝም ማለቱ ደረጃቸው ለኣዘገጡ በኮምፕዩተር ለቀረቡ ጽሑፎች ኣስተዋጽዖ እያበረከተ ነው።
 
፲፫. ኣንድ ኣንባቢ ኮምፕዩተር፣ የእጅ ስልክና የመሳሰሉት ላይ የሚመለከተው የግዕዝ ዩኒኮድ ፊደል መሣሪያው ላይ በኣለው ፊደል ነው። ፊደሉ ትክክል ከኣልሆነ ትክክል ኣለመሆኑንንም ላይረዳ ይችላል። ለምሳሌ ያህል የ"ጨ" ቀለበቶች ሁለት ናቸው ቢባልና ቢያነብ ባለ ሁለት ቀለበቶች ትክክለኛ ፊደል ከሌለው ፊደሉን የሚያነበው ሦስት ቀለበቶች በኣሉት የተሳሳተ ፊደል ነው።
 
===ትርጕሞች===