ከ«የማቴዎስ ወንጌል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 1,551፦
66፤እነርሱም፡ኼደው፡ከጠባቂዎች፡ጋራ፡ድንጋዩን፡ዐትመው፡መቃብሩን፡አስጠበቁ።
== '''ምዕራፍ ፳፰''' ==
1፤በሰንበትም፡መጨረሻ፡መዠመሪያው፡ቀን፡ሲነጋ፡መግደላዊት፡ማርያምና፡ኹለተኛዪቱ፡ማርያም፡
መቃብሩን፡ሊያዩ፡መጡ።
2፤እንሆም፥የጌታ፡መልአክ፡ከሰማይ፡ስለ፡ወረደ፡ታላቅ፡የምድር፡መናወጥ፡ኾነ፤ቀርቦም፡ድንጋዩን፡
አንከባሎ፡በላዩ፡ተቀመጠ።
3፤መልኩም፡እንደ፡መብረቅ፡ልብሱም፡እንደ፡በረዶ፡ነጭ፡ነበረ።
4፤ጠባቂዎቹም፡ርሱን፡ከመፍራት፡የተነሣ፡ተናወጡ፡እንደ፡ሞቱም፡ኾኑ።
5፤መልአኩም፡መልሶ፡ሴቶቹን፡አላቸው፦እናንተስ፡አትፍሩ፥የተሰቀለውን፡ኢየሱስን፡እንድትሹ፡
ዐውቃለኹና፤
6፤እንደ፡ተናገረ፡ተነሥቷልና፥በዚህ፡የለም፤የተኛበትን፡ስፍራ፡ኑና፡እዩ።
7፤ፈጥናችኹም፡ኺዱና፦ከሙታን፡ተነሣ፥እንሆም፥ወደ፡ገሊላ፡ይቀድማችዃል፡በዚያም፡ታዩታላችኹ፡
ብላችኹ፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ንገሯቸው።እንሆም፥ነገርዃችኹ።
8፤በፍርሀትና፡በታላቅ፡ደስታም፡ፈጥነው፡ከመቃብር፡ኼዱ፥ለደቀ፡መዛሙርቱም፡ሊያወሩ፡ሮጡ።
9፤እንሆም፥ኢየሱስ፡አገኛቸውና፦ደስ፡ይበላችኹ፡አላቸው።እነርሱም፡ቀርበው፡እግሩን፡ይዘው፡ሰገዱለት።
10፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፦አትፍሩ፤ኼዳችኹ፡ወደ፡ገሊላ፡እንዲኼዱ፡ለወንድሞቼ፡ተናገሩ፥በዚያም፡
ያዩኛል፡አላቸው።
11፤ሲኼዱም፡ሳሉ፥እንሆ፥ከጠባቂዎቹ፡አንዳንድ፡ወደ፡ከተማ፡መጥተው፡የኾነውን፡ዅሉ፡ለካህናት፡
አለቃዎች፡አወሩ።
12፤ከሽማግሌዎች፡ጋራም፡ተሰብስበው፡ተማከሩና፡ለጭፍራዎች፡ብዙ፡ገንዘብ፡ሰጥተዋቸው።
13፤እኛ፡ተኝተን፡ሳለን፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡በሌሊት፡መጥተው፡ሰረቁት፡በሉ።
14፤ይህም፡በገዢው፡ዘንድ፡የተሰማ፡እንደ፡ኾነ፥እኛ፡እናስረዳዋለን፡እናንተም፡ያለሥጋት፡እንድትኾኑ፡
እናደርጋለን፡አሏቸው።
15፤እነርሱም፡ገንዘቡን፡ተቀብለው፡እንዳስተማሯቸው፡አደረጉ።ይህም፡ነገር፡በአይሁድ፡ዘንድ፡እስከ፡ዛሬ፡
ድረስ፡ሲወራ፡ይኖራል።
16፤ዐሥራ፡አንዱ፡ደቀ፡መዛሙርት፡ግን፡ኢየሱስ፡ወዳዘዛቸው፡ተራራ፡ወደ፡ገሊላ፡ኼዱ፥
17፤ባዩትም፡ጊዜ፡ሰገዱለት፤የተጠራጠሩ፡ግን፡ነበሩ።
18፤ኢየሱስም፡ቀረበና፡እንዲህ፡ብሎ፡ተናገራቸው፦ሥልጣን፡ዅሉ፡በሰማይና፡በምድር፡ተሰጠኝ።
19-20፤እንግዲህ፡ኺዱና፡አሕዛብን፡ዅሉ፡በአብ፡በወልድና፡በመንፈስ፡ቅዱስ፡ስም፡
እያጠመቃችዃቸው፥ያዘዝዃችኹንም፡ዅሉ፡እንዲጠብቁ፡እያስተማራችዃቸው፡ደቀ፡መዛሙርት፡
አድርጓቸው፤እንሆም፡እኔ፡እስከ፡ዓለም፡ፍጻሜ፡ድረስ፡ዅልጊዜ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ነኝ፨