ከ«የማቴዎስ ወንጌል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 1,353፦
46፤እነዚያም፡ወደዘለዓለም፡ቅጣት፥ጻድቃን፡ግን፡ወደዘለዓለም፡ሕይወት፡ይኼዳሉ።
== '''ምዕራፍ ፳፮''' ==
1፤ኢየሱስም፡እነዚህን፡ቃሎች፡ዅሉ፡በፈጸመ፡ጊዜ፥
2፤ለደቀ፡መዛሙርቱ፦ከኹለት፡ቀን፡በዃላ፡ፋሲካ፡እንዲኾን፡ታውቃላችኹ፥የሰው፡ልጅም፡ሊሰቀል፡
ዐልፎ፡ይሰጣል፡አለ።
3፤በዚያን፡ጊዜ፡የካህናት፡አለቃዎች፡የሕዝብም፡ሽማግሌዎች፡ቀያፋ፡በሚባለው፡በሊቀ፡ካህናቱ፡ግቢ፡
ተሰበሰቡ፥
4፤ኢየሱስንም፡በተንኰል፡ሊያስይዙት፡ሊገድሉትም፡ተማከሩ፤
5፤ነገር፡ግን፦በሕዝቡ፡ዘንድ፡ሁከት፡እንዳይነሣ፡በበዓል፡አይኹን፡አሉ።
6፤ኢየሱስም፡በቢታንያ፡በለምጻሙ፡በስምዖን፡ቤት፡ሳለ፥
7፤አንዲት፡ሴት፡ዋጋው፡እጅግ፡የበዛ፡ሽቱ፡የሞላው፡የአልባስጥሮስ፡ብልቃጥ፡ይዛ፡ወደ፡ርሱ፡ቀረበች፡
በማእዱም፡ተቀምጦ፡ሳለ፡በራሱ፡ላይ፡አፈሰሰችው።
8፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ይህን፡አይተው፡ተቈጡና፦ይህ፡ጥፋት፡ለምንድር፡ነው፧
9፤ይህ፡በብዙ፡ዋጋ፡ተሽጦ፡ለድኻዎች፡ሊሰጥ፡ይቻል፡ነበርና፥አሉ።
10፤ኢየሱስም፡ይህን፡ዐውቆ፡እንዲህ፡አላቸው፦መልካም፡ሥራ፡ሠርታልኛለችና፡ሴቲቱንስ፡ስለ፡ምን፡
ታደክሟታላችኹ፧
11፤ድኻዎች፡ዅልጊዜ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ይኖራሉና፥እኔ፡ግን፡ዅልጊዜ፡ከእናንተ፡ጋራ፡አልኖርም፤
12፤ርሷ፡ይህን፡ሽቱ፡በሰውነቴ፡ላይ፡አፍሳ፟፡ለመቃብሬ፡አደረገች።
13፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ይህ፡ወንጌል፡በዓለም፡ዅሉ፡በማናቸውም፡ስፍራ፡በሚሰበክበት፡ርሷ፡ያደረገችው፡
ደግሞ፡ለርሷ፡መታሰቢያ፡እንዲኾን፡ይነገራል።
14፤በዚያን፡ጊዜ፡የአስቆሮቱ፡ይሁዳ፡የሚባለው፡ከዐሥራ፡ኹለቱ፡አንዱ፡ወደካህናት፡አለቃዎች፡ኼዶ፦
15፤ምን፡ልትሰጡኝ፡ትወዳላችኹ፡እኔም፡አሳልፌ፡እሰጣችዃለኹ፧እነርሱም፡ሠላሳ፡ብር፡መዘኑለት።
16፤ከዚያችም፡ሰዓት፡ዠምሮ፡አሳልፎ፡ሊሰጠው፡ምቹ፡ጊዜ፡ይሻ፡ነበር።
17፤በቂጣው፡በዓል፡በመዠመሪያ፡ቀን፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ወደ፡ኢየሱስ፡ቀርበው፦ፋሲካን፡ትበላ፡ዘንድ፡
ወዴት፡ልናሰናዳልኽ፡ትወዳለኽ፡አሉት።
18፤ርሱም፦ወደ፡ከተማ፡ከእገሌ፡ዘንድ፡ኼዳችኹ፦መምህር፦ጊዜዬ፡ቀርቧል፤ከደቀ፡መዛሙርቴ፡ጋራ፡
ከአንተ፡ዘንድ፡ፋሲካን፡አደርጋለኹ፡ይላል፡በሉት፡አለ።
19፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ኢየሱስ፡እንዳዘዛቸው፡አደረጉ፡ፋሲካንም፡አሰናዱ።
20፤በመሸም፡ጊዜ፡ከዐሥራ፡ኹለቱ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ጋራ፡በማእዱ፡ተቀመጠ።
21፤ሲበሉም፦እውነት፡እላችዃለኹ፥ከእናንተ፡አንዱ፡እኔን፡አሳልፎ፡ይሰጣል፡አለ።
22፤እጅግም፡አዝነው፡እያንዳንዱ፦ጌታ፡ሆይ፥እኔ፡እኾንን፧ይሉት፡ዠመር።
23፤ርሱም፡መልሶ፦ከእኔ፡ጋራ፡እጁን፡በወጭቱ፡ያጠለቀ፥እኔን፡አሳልፎ፡የሚሰጥ፡ርሱ፡ነው።
24፤የሰው፡ልጅስ፡ስለ፡ርሱ፡እንደ፡ተጻፈ፡ይኼዳል፥ነገር፡ግን፥የሰው፡ልጅ፡ዐልፎ፡ለሚሰጥበት፡ለዚያ፡
ሰው፡ወዮለት፤ያ፡ሰው፡ባልተወለደ፡ይሻለው፡ነበር፡አለ።
25፤አሳልፎ፡የሚሰጠው፡ይሁዳም፡መልሶ፦መምህር፡ሆይ፥እኔ፡እኾንን፧አለ፤አንተ፡አልኽ፡አለው።
26፤ሲበሉም፡ኢየሱስ፡እንጀራን፡አንሥቶ፡ባረከ፡ቈርሶም፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ሰጠና፦እንካችኹ፥ብሉ፡ይህ፡
ሥጋዬ፡ነው፡አለ።
27፤ጽዋንም፡አንሥቶ፡አመስግኖም፡ሰጣቸው፡እንዲህም፡አለ፦ዅላችኹ፡ከርሱ፡ጠጡ፤
28፤ስለ፡ብዙዎች፡ለኀጢአት፡ይቅርታ፡የሚፈስ፡የዐዲስ፡ኪዳን፡ደሜ፡ይህ፡ነው።
29፤ነገር፡ግን፥እላችዃለኹ፥በአባቴ፡መንግሥት፡ከእናንተ፡ጋራ፡ከዚህ፡ከወይን፡ፍሬ፡ዐዲሱን፡
እስከምጠጣበት፡እስከዚያ፡ቀን፡ድረስ፡ከዛሬ፡ዠምሬ፡አልጠጣውም።
30፤መዝሙርም፡ከዘመሩ፡በዃላ፡ወደ፡ደብረ፡ዘይት፡ወጡ።
31፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፦በዚች፡ሌሊት፡ዅላችኹ፡በእኔ፡ትሰናከላላችኹ፤እረኛውን፡እመታለኹ፡
የመንጋውም፡በጎች፡ይበተናሉ፡የሚል፡ተጽፏልና፤
32፤ከተነሣኹ፡በዃላ፡ግን፡ወደ፡ገሊላ፡እቀድማችዃለኹ፡አላቸው።
33፤ጴጥሮስም፡መልሶ፦ዅሉም፡ባንተ፡ቢሰናከሉ፡እኔ፡ከቶ፡አልሰናከልም፡አለው።
34፤ኢየሱስ፦እውነት፡እልኻለኹ፥በዚች፡ሌሊት፡ዶሮ፡ሳይጮኽ፡ሦስት፡ጊዜ፡ትክደኛለኽ፡አለው።
35፤ጴጥሮስ፦ከአንተ፡ጋራ፡መሞት፡እንኳ፡የሚያስፈልገኝ፡ቢኾን፥ከቶ፡አልክድኽም፡አለው።ደቀ፡
መዛሙርቱ፡ዅሉ፡ደግሞ፡እንደዚሁ፡አሉ።
36፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡ከነርሱ፡ጋራ፡ጌቴሴማኒ፡ወደምትባል፡ስፍራ፡መጣ፡ደቀ፡መዛሙርቱንም፦ወዲያ፡
ኼጄ፡ስጸልይ፡ሳለ፡በዚህ፡ተቀመጡ፡አላቸው።
37፤ጴጥሮስንም፡ኹለቱንም፡የዘብዴዎስን፡ልጆች፡ወስዶ፡ሊያዝን፡ሊተክዝም፡ዠመር።
38፤ነፍሴ፡እስከ፡ሞት፡ድረስ፡እጅግ፡ዐዘነች፤በዚህ፡ቈዩ፥ከእኔም፡ጋራ፡ትጉ፡አላቸው።
39፤ጥቂትም፡ወደ፡ፊት፡እልፍ፡ብሎ፡በፊቱ፡ወደቀና፡ሲጸልይ፦አባቴ፥ቢቻልስ፥ይህች፡ጽዋ፡ከእኔ፡
ትለፍ፤ነገር፡ግን፥አንተ፡እንደምትወድ፡ይኹን፡እንጂ፡እኔ፡እንደምወድ፡አይኹን፡አለ።
40፤ወደ፡ደቀ፡መዛሙርቱም፡መጣ፤ተኝተውም፡አገኛቸውና፡ጴጥሮስን፦እንዲሁም፡ከእኔ፡ጋራ፡አንዲት፡
ሰዓት፡እንኳ፡ልትተጉ፡አልቻላችኹምን፧
41፤ወደ፡ፈተና፡እንዳትገቡ፡ትጉና፡ጸልዩ፤መንፈስስ፡ተዘጋጅታለች፡ሥጋ፡ግን፡ደካማ፡ነው፡አለው።
42፤ደግሞ፡ኹለተኛ፡ኼዶ፡ጸለየና፦አባቴ፥ይህች፡ጽዋ፡ሳልጠጣት፡ታልፍ፡ዘንድ፡የማይቻል፡እንደ፡
ኾነ፥ፈቃድኽ፡ትኹን፡አለ።
43፤ደግሞም፡መጥቶ፡ዐይኖቻቸው፡በእንቅልፍ፡ከብደው፡ነበርና፥ተኝተው፡አገኛቸው።
44፤ደግሞም፡ትቷቸው፡ኼደ፥ሦስተኛም፡ያንኑ፡ቃል፡ደግሞ፡ጸለየ።
45፤ከዚያ፡ወዲያ፡ወደ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡መጥቶ፦እንግዲህስ፡ተኙ፡ዕረፉም፤እንሆ፥ሰዓቲቱ፡ቀርባለች፡
የሰው፡ልጅም፡በኀጢአተኛዎች፡እጅ፡ዐልፎ፡ይሰጣል።
46፤ተነሡ፥እንኺድ፤እንሆ፥አሳልፎ፡የሚሰጠኝ፡ቀርቧል፡አላቸው።
47፤ይህንም፡ገና፡ሲናገር፥እንሆ፥ከዐሥራ፡ኹለቱ፡አንዱ፡ይሁዳ፡መጣ፥ከርሱም፡ጋራ፡ብዙ፡ሕዝብ፡
ሰይፍና፡ጐመድ፡ይዘው፡ከካህናት፡አለቃዎችና፡ከሕዝቡ፡ሽማግሌዎች፡ዘንድ፡መጡ።
48፤አሳልፎ፡የሚሰጠውም፦የምስመው፡ርሱ፡ነው፤ያዙት፡ብሎ፡ምልክት፡ሰጥቷቸው፡ነበር።
49፤ወዲያውም፡ወደ፡ኢየሱስ፡ቀረበና፦መምህር፡ሆይ፥ሰላም፡ለአንተ፡ይኹን፡ብሎ፡ሳመው።
50፤ኢየሱስም፦ወዳጄ፡ሆይ፥ለምን፡ነገር፡መጣኽ፧አለው።በዚያን፡ጊዜ፡ቀረቡ፡እጃቸውንም፡በኢየሱስ፡
ላይ፡ጭነው፡ያዙት።
51፤እንሆም፥ከኢየሱስ፡ጋራ፡ከነበሩት፡አንዱ፡እጁን፡ዘርግቶ፡ሰይፉን፡መዘዘና፡የሊቀ፡ካህናቱን፡ባሪያ፡መቶ፟፡
ዦሮውን፡ቈረጠው።
52፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡እንዲህ፡አለው፦ሰይፍ፡የሚያነሡ፡ዅሉ፡በሰይፍ፡ይጠፋሉና፡ሰይፍኽን፡ወደ፡
ስፍራው፡መልስ።
53፤ወይስ፡አባቴን፡እንድለምን፡ርሱም፡አኹን፡ከዐሥራ፡ኹለት፡ጭፍራዎች፡የሚበዙ፡መላእክት፡
እንዲሰድልኝ፡የማይቻል፡ይመስልኻልን፧
54፤እንዲህ፡ከኾነስ፦እንደዚህ፡ሊኾን፡ይገ፟ባ፟ል፡የሚሉ፡መጻሕፍት፡እንዴት፡ይፈጸማሉ፧
55፤በዚያን፡ሰዓት፡ኢየሱስ፡ለሕዝቡ፦ወንበዴን፡እንደምትይዙ፡ሰይፍና፡ጐመድ፡ይዛችኹ፡ልትይዙኝ፡
ወጣችኹን፧በመቅደስ፡ዕለት፡ዕለት፡እያስተማርኹ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ስቀመጥ፡ሳለኹ፡አልያዛችኹኝም።
56፤ነገር፡ግን፥ይህ፡ዅሉ፡የኾነ፡የነቢያት፡መጻሕፍት፡ይፈጸሙ፡ዘንድ፡ነው፡አለ።በዚያን፡ጊዜ፡ደቀ፡
መዛሙርቱ፡ዅሉ፡ትተውት፡ሸሹ።
57፤ኢየሱስን፡የያዙትም፡ጻፊዎችና፡ሽማግሌዎች፡ወደተከማቹበት፡ወደ፡ሊቀ፡ካህናቱ፡ወደ፡ቀያፋ፡ወሰዱት።
58፤ጴጥሮስ፡ግን፡እስከሊቀ፡ካህናቱ፡ግቢ፡ድረስ፡ሩቅ፡ኾኖ፡ተከተለው፥የነገሩንም፡ፍጻሜ፡ያይ፡ዘንድ፡
ወደ፡ውስጥ፡ገብቶ፡ከሎሌዎቹ፡ጋራ፡ተቀመጠ።
59፤የካህናት፡አለቃዎችና፡ሽማግሌዎች፡ሸንጎውም፡ዅሉ፡እንዲገድሉት፡በኢየሱስ፡ላይ፡የሐሰት፡ምስክር፡
ይፈልጉ፡ነበር፥አላገኙም፤
60፤ብዙም፡የሐሰት፡ምስክሮች፡ምንም፡ቢቀርቡ፡አላገኙም።
61፤በዃላም፡ኹለት፡ቀርበው፦ይህ፡ሰው፦የእግዚአብሔርን፡ቤተ፡መቅደስ፡አፍርሼ፡በሦስት፡ቀን፡
ልሠራው፡እችላለኹ፡ብሏል፡አሉ።
62፤ሊቀ፡ካህናቱም፡ተነሥቶ፦እነዚህ፡ለሚመሰክሩብኽ፡አንድ፡ስንኳ፡አትመልስምን፧አለው።
63፤ኢየሱስ፡ግን፡ዝም፡አለ።ሊቀ፡ካህናቱም፦አንተ፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡ክርስቶስ፡የኾንኽ፡እንደ፡ኾነ፡
እንድትነግረን፡በሕያው፡እግዚአብሔር፡አምልኻለኹ፡አለው።
64፤ኢየሱስም፦አንተ፡አልኽ፥ነገር፡ግን፥እላችዃለኹ፥ከእንግዲህ፡ወዲህ፡የሰው፡ልጅ፡በኀይል፡ቀኝ፡
ሲቀመጥ፥በሰማይም፡ደመና፡ሲመጣ፡ታያላችኹ፡አለው።
65፤በዚያን፡ጊዜ፡ሊቀ፡ካህናቱ፡ልብሱን፡ቀዶ፦ተሳድቧል፡እንግዲህ፡ወዲህ፡ምስክሮች፡ስለ፡ምን፡
ያስፈልገናል፧እንሆ፥ስድቡን፡አኹን፡ሰምታችዃል፤ምን፡ይመስላችዃል፧አለ።
66፤እነርሱም፦ሞት፡ይገ፟ባ፟ዋል፡ብለው፡መለሱ።
67፤በዚያን፡ጊዜ፡በፊቱ፡ተፉበት፤ጐሰሙትም፥ሌላዎችም፡በጥፊ፡መትተው፦ክርስቶስ፡ሆይ፥በጥፊ፡
የመታኽ፡ማን፡ነው፧
68፤ትንቢት፡ተናገርልን፡አሉ።
69፤ጴጥሮስም፡ከቤት፡ውጭ፡በዐጥሩ፡ግቢ፡ተቀምጦ፡ነበር፤አንዲት፡ገረድም፡ወደ፡ርሱ፡ቀርባ፦አንተ፡
ደግሞ፡ከገሊላው፡ከኢየሱስ፡ጋራ፡ነበርኽ፡አለችው።
70፤ርሱ፡ግን፦የምትዪውን፡አላውቀውም፡ብሎ፡በዅሉ፡ፊት፡ካደ።
71፤ወደ፡በሩም፡ሲወጣ፡ሌላዪቱ፡አየችውና፡በዚያ፡ላሉት፦ይህ፡ደግሞ፡ከናዝሬቱ፡ከኢየሱስ፡ጋራ፡ነበረ፡
አለች።
72፤ዳግመኛም፡ሲምል።ሰውየውን፡አላውቀውም፡ብሎ፡ካደ።
73፤ጥቂትም፡ቈይተው፡በዚያ፡ቆመው፡የነበሩ፡ቀርበው፡ጴጥሮስን፦አነጋገርኽ፡ይገልጥኻልና፥በእውነት፡
አንተ፡ደግሞ፡ከነርሱ፡ወገን፡ነኽ፡አሉት።
74፤በዚያን፡ጊዜ፦ሰውየውን፡አላውቀውም፡ብሎ፡ሊራገምና፡ሊምል፡ዠመረ።ወዲያውም፡ዶሮ፡ጮኸ።
75፤ጴጥሮስም፦ዶሮ፡ሳይጮኽ፡ሦስት፡ጊዜ፡ትክደኛለኽ፡ያለው፡የኢየሱስ፡ቃል፡ትዝ፡አለው፤ወደ፡
ውጭም፡ወጥቶ፡መራራ፡ልቅሶ፡አለቀሰ።
== '''ምዕራፍ ፳፯''' ==