ከ«የማቴዎስ ወንጌል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 1,151፦
46፤አንድም፡ቃል፡ስንኳ፡ይመልስለት፡ዘንድ፡የተቻለው፡የለም፥ከዚያ፡ቀንም፡ዠምሮ፡ወደ፡ፊት፡ማንም፡ሊጠይቀው፡አልደፈረም።
== '''ምዕራፍ ፳፫''' ==
1፤በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡ለሕዝቡና፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡እንዲህ፡ብሎ፡ነገራቸው፦
2፤ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፡በሙሴ፡ወንበር፡ተቀምጠዋል።
3፤ስለዚህ፥ያዘዟችኹን፡ዅሉ፡አድርጉ፥ጠብቁትም፤ነገር፡ግን፥እየተናገሩ፡አያደርጉትምና፥እንደ፡ሥራቸው፡
አታድርጉ።
4፤ከባድና፡አስቸጋሪ፡ሸክም፡ተብትበው፡በሰው፡ትከሻ፡ይጭናሉ፥እነርሱ፡ግን፡በጣታቸው፡ስንኳ፡ሊነኩት፡
አይወዱም።
5፤ለሰውም፡እንዲታዩ፡ሥራቸውን፡ዅሉ፡ያደርጋሉ፤ስለዚህ፥ዐሸን፡ክታባቸውን፡ያሰፋሉ፥ዘርፉንም፡
ያስረዝማሉ፥
6፤በምሳም፡የከበሬታ፡ስፍራ፥በምኵራብም፡የከበሬታ፡ወንበር፥
7፤በገበያም፡ሰላምታና፦መምህር፡ሆይ፡መምህር፡ሆይ፡ተብለው፡እንዲጠሩ፡ይወዳሉ።
8፤እናንተ፡ግን፦መምህር፡ተብላችኹ፡አትጠሩ፤መምህራችኹ፡አንድ፡ስለ፡ኾነ፡እናንተም፡ዅላችኹ፡
ወንድማማች፡ናችኹ።
9፤አባታችኹ፡አንዱ፡ርሱም፡የሰማዩ፡ነውና፥በምድር፡ላይ፡ማንንም፦አባት፡ብላችኹ፡አትጥሩ።
10፤ሊቃችኹ፡አንድ፡ርሱም፡ክርስቶስ፡ነውና፦ሊቃውንት፡ተብላችኹ፡አትጠሩ።
11፤ከእናንተም፡የሚበልጠው፡አገልጋያችኹ፡ይኾናል።
12፤ራሱን፡ከፍ፡የሚያደርግ፡ዅሉ፡ይዋረዳል፥ራሱንም፡የሚያዋርድ፡ዅሉ፡ከፍ፡ይላል።
13፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥መንግሥተ፡ሰማያትን፡በሰው፡ፊት፡ስለምትዘጉ፥ወዮላችኹ፡
እናንተ፡አትገቡም፡የሚገቡትንም፡እንዳይገቡ፡ትከለክላላችኹ።
14፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥በጸሎት፡ርዝመት፡እያመካኛችኹ፡የመበለቶችን፡ቤት፡
ስለምትበሉ፥ወዮላችኹ፤ስለዚህ፥የባሰ፡ፍርድ፡ትቀበላላችኹ።
15፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥አንድ፡ሰው፡ልታሳምኑ፡በባሕርና፡በደረቅ፡ስለምትዞሩ፥በኾነም፡
ጊዜ፡ከእናንተ፡ይልቅ፡ኹለት፡ዕጥፍ፡የባሰ፡የገሃነም፡ልጅ፡ስለምታደርጉት፥ወዮላችኹ።
16፤እናንተ፦ማንም፡በቤተ፡መቅደስ፡የሚምል፡ምንም፡የለበትም፤ማንም፡በቤተ፡መቅደስ፡ወርቅ፡የሚምል፡
ግን፡በመሐላው፡ይያዛል፡የምትሉ፥ዕውሮች፡መሪዎች፥ወዮላችኹ።
17፤እናንተ፡ደንቈሮዎችና፡ዕውሮች፥ማናቸው፡ይበልጣል፧ወርቁ፡ነውን፧ወይስ፡ወርቁን፡የቀደሰው፡ቤተ፡
መቅደስ፧
18፤ደግማችኹም፦ማንም፡በመሠዊያው፡የሚምል፡ምንም፡የለበትም፤ማንም፡በላዩ፡ባለው፡መባ፡የሚምል፡
ግን፡በመሐላው፡ይያዛል፡ትላላችኹ።
19፤እናንተ፡ደንቈሮዎችና፡ዕውሮች፥ማናቸው፡ይበልጣል፧መባው፡ነውን፧ወይስ፡መባውን፡የሚቀድሰው፡
መሠዊያው፧
20፤እንግዲህ፡በመሠዊያው፡የሚምለው፡በርሱና፡በርሱ፡ላይ፡ባለው፡ዅሉ፡ይምላል፤
21፤በቤተ፡መቅደስም፡የሚምለው፡በርሱና፡በርሱ፡በሚኖረው፡ይምላል፤
22፤በሰማይም፡የሚምለው፡በእግዚአብሔር፡ዙፋንና፡በርሱ፡ላይ፡በተቀመጠው፡ይምላል።
23፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥ከአዝሙድና፡ከእንስላል፡ከከሙንም፡ዓሥራት፡
ስለምታወጡ፥ፍርድንና፡ምሕረትን፡ታማኝነትንም፥በሕግ፡ያለውን፡ዋና፡ነገር፡
ስለምትተዉ፥ወዮላችኹ፤ሌላውን፡ሳትተዉ፡ይህን፡ልታደርጉ፡ይገ፟ባ፟ችኹ፡ነበር።
24፤እናንተ፡ዕውሮች፡መሪዎች፥ትንኝን፡የምታጠሩ፡ግመልንም፡የምትውጡ።
25፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥በውስጡ፡ቅሚያና፡ሥሥት፡ሞልቶ፡ሳለ፡የጽዋውንና፡የወጭቱን፡
ውጭ፡ስለምታጠሩ፥ወዮላችኹ።
26፤አንተ፡ዕውር፡ፈሪሳዊ፥ውጭው፡ደግሞ፡ጥሩ፡እንዲኾን፡አስቀድመኽ፡የጽዋውንና፡የወጭቱን፡ውስጡን፡
አጥራ።
27፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥በውጭ፡አምረው፡የሚታዩ፡በውስጡ፡ግን፡የሙታን፡ዐጥንት፡
ርኵሰትም፡ዅሉ፡የተሞሉ፡በኖራ፡የተለሰኑ፡መቃብሮችን፡ስለምትመስሉ፥ወዮላችኹ።
28፤እንዲሁ፡እናንተ፡ደግሞ፡በውጭ፡ለሰው፡እንደ፡ጻድቃን፡ትታያላችኹ፥በውስጣችኹ፡ግን፡ግብዝነትና፡
ዐመፀኝነት፡ሞልቶባችዃል።
29፤እናንተ፡ግብዞች፡ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያን፥የነቢያትን፡መቃብር፡ስለምትሠሩ፡የጻድቃንንም፡መቃብር፡
ስለምታስጌጡና፦
30፤በአባቶቻችን፡ዘመን፡ኖረን፡በኾነስ፥በነቢያት፡ደም፡ባልተባበርናቸውም፡ነበር፡ስለምትሉ፥ወዮላችኹ።
31፤እንግዲያስ፡የነቢያት፡ገዳዮች፡ልጆች፡እንደኾናችኹ፡በራሳችኹ፡ላይ፡ትመሰክራላችኹ።
32፤እናንተ፡ደግሞ፡የአባቶቻችኹን፡መስፈሪያ፡ሙሉ።
33፤እናንተ፡እባቦች፥የእፍኝት፡ልጆች፥ከገሃነም፡ፍርድ፡እንዴት፡ታመልጣላችኹ፧
34፤ስለዚህ፥እንሆ፥ነቢያትንና፡ጥበበኛዎችን፡ጻፊዎችንም፡ወደ፡እናንተ፡እልካለኹ፤ከነርሱም፡ትገድላላችኹ፡
ትሰቅሉማላችኹ፥ከነርሱም፡በምኵራባችኹ፡ትገርፋላችኹ፡ከከተማም፡ወደ፡ከተማ፡ታሳድዳላችኹ፤
35፤ከጻድቁ፡ከአቤል፡ደም፡ዠምሮ፡በቤተ፡መቅደስና፡በመሠዊያው፡መካከል፡እስከገደላችኹት፡እስከበራክዩ፡
ልጅ፡እስከዘካርያስ፡ደም፡ድረስ፡በምድር፡ላይ፡የፈሰሰው፡የጻድቅ፡ደም፡ዅሉ፡ይደርስባችኹ፡ዘንድ።
36፤እውነት፡እላችዃለኹ፥ይህ፡ዅሉ፡በዚህ፡ትውልድ፡ላይ፡ይደርሳል።
37፤ኢየሩሳሌም፡ኢየሩሳሌም፡ሆይ፥ነቢያትን፡የምትገድል፡ወደ፡ርሷ፡የተላኩትንም፡የምትወግር፥ዶሮ፡
ጫጩቶቿን፡ከክንፎቿ፡በታች፡እንደምትሰበስብ፡ልጆችሽን፡እሰበስብ፡ዘንድ፡ስንት፡ጊዜ፡ወደድኹ!
አልወደዳችኹምም።
38፤እንሆ፥ቤታችኹ፡የተፈታ፡ኾኖ፡ይቀርላችዃል።
39፤እላችዃለኹና፥በጌታ፡ስም፡የሚመጣ፡የተባረከ፡ነው፡እስክትሉ፡ድረስ፡ከእንግዲህ፡ወዲህ፡አታዩኝም።
== '''ምዕራፍ ፳፬''' ==