ከ«የማቴዎስ ወንጌል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 1,025፦
34፤ኢየሱስም፡ዐዘነላቸውና፡ዐይኖቻቸውን፡ዳሰሰ፥ወዲያውም፡አዩና፡ተከተሉት።
== '''ምዕራፍ ፳፩''' ==
1፤ወደ፡ኢየሩሳሌምም፡ቀርበው፡ወደ፡ደብረ፡ዘይት፡ወደ፡ቤተ፡ፋጌ፡ሲደርሱ፥ያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡ከደቀ፡
መዛሙርቱ፡ኹለት፡ላከ፥
2፤እንዲህም፡አላቸው፦በፊታችኹ፡ወዳለችው፡መንደር፡ኺዱ፥በዚያን፡ጊዜም፡የታሰረችን፡አህያ፡
ውርንጫም፡ከርሷ፡ጋራ፡ታገኛላችኹ፤ፈታ፟ችኹ፡አምጡልኝ።
3፤ማንም፡አንዳች፡ቢላችኹ፦ለጌታ፡ያስፈልጉታል፡በሉ፤ወዲያውም፡ይሰዳቸዋል።
4-5፤ለጽዮን፡ልጅ፦እንሆ፥ንጉሥሽ፡የዋህ፡ኾኖ፡በአህያ፡ላይና፡በአህያዪቱ፡ግልገል፡በውርንጫዪቱ፡ላይ፡
ተቀምጦ፡ወደ፡አንቺ፡ይመጣል፡በሏት፡ተብሎ፡በነቢይ፡የተነገረው፡ይፈጸም፡ዘንድ፡ይህ፡ኾነ።
6፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ኼደው፡ኢየሱስ፡እንዳዘዛቸው፡አደረጉ፥
7፤አህያዪቱንና፡ውርንጫዋንም፡አመጡለት፥ልብሳቸውንም፡በእነርሱ፡ላይ፡ጫኑ፥ተቀመጠባቸውም።
8፤ከሕዝቡም፡እጅግ፡ብዙዎች፡ልብሳቸውን፡በመንገድ፡ላይ፡አነጠፉ፥ሌላዎችም፡ከዛፍ፡ጫፍ፡ጫፉን፡
እየቈረጡ፡በመንገድ፡ላይ፡ያነጥፉ፡ነበር።
9፤የሚቀድሙትም፡ሕዝብ፡የሚከተሉትም፦ሆሣዕና፡ለዳዊት፡ልጅ፡በጌታ፡ስም፡የሚመጣ፡የተባረከ፡
ነው፤ሆሣዕና፡በአርያም፡እያሉ፡ይጮኹ፡ነበር።
10፤ወደ፡ኢየሩሳሌምም፡በገባ፡ጊዜ፡መላው፡ከተማ፦ይህ፡ማን፡ነው፧ብሎ፡ተናወጠ።
11፤ሕዝቡም፦ይህ፡ከገሊላ፡ናዝሬት፡የመጣ፡ነቢዩ፡ኢየሱስ፡ነው፡አሉ።
12፤ኢየሱስም፡ወደ፡መቅደስ፡ገባና፡በመቅደስ፡የሚሸጡትንና፡የሚገዙትን፡ዅሉ፡አወጣ፥የገንዘብ፡
ለዋጮችንም፡ገበታዎች፡የርግብ፡ሻጪዎችንም፡ወንበሮች፡ገለበጠና፦
13፤ቤቴ፡የጸሎት፡ቤት፡ትባላለች፡ተብሎ፡ተጽፏል፥እናንተ፡ግን፡የወንበዴዎች፡ዋሻ፡አደረጋችዃት፡
አላቸው።
14፤በመቅደስም፡ዕውሮችና፡ዐንካሳዎች፡ወደ፡ርሱ፡ቀረቡና፡ፈወሳቸው።
15፤ነገር፡ግን፥የካህናት፡አለቃዎችና፡ጻፊዎች፡ያደረገውን፡ድንቃ፡ድንቅ፡በመቅደስም፦ሆሣዕና፡ለዳዊት፡ልጅ፡እያሉ፡የሚጮኹትን፡ልጆች፡ባዩ፡ጊዜ፥ተቈጥተው።
16፤እነዚህ፡የሚሉትን፡አትሰማምን፧አሉት።ኢየሱስም፦እሰማለኹ፤ከሕፃናትና፡ከሚጠቡት፡አፍ፡ምስጋናን፡
ለራስኽ፡አዘጋጀኽ፡የሚለውን፡ቃል፡ከቶ፡አላነበባችኹምን፧አላቸው።
17፤ትቷቸውም፡ከከተማ፡ወደ፡ቢታንያ፡ወጣ፡በዚያም፡ዐደረ።
18፤በማለዳም፡ወደ፡ከተማ፡ሲመለስ፡ተራበ።
19፤በመንገድም፡አጠገብ፡በለስ፡አይቶ፡ወደ፡ርሷ፡መጣ፤ከቅጠልም፡ብቻ፡በቀር፡ምንም፡
አላገኘባትምና፦ለዘለዓለሙ፡ፍሬ፡አይገኝብሽ፡አላት።በለሲቱም፡ያን፡ጊዜውን፡ደረቀች።
20፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ይህን፡አይተው፦በለሲቱ፡ያን፡ጊዜውን፡እንዴት፡ደረቀች፧ብለው፡ተደነቁ።
21፤ኢየሱስም፡መልሶ፦እውነት፡እላችዃለኹ፥እምነት፡ቢኖራችኹ፡ባትጠራጠሩም፥በበለሲቱ፡እንደ፡ኾነባት፡
ብቻ፡አታደርጉም፤ነገር፡ግን፥ይህን፡ተራራ፡እንኳ፦ተነቅለኽ፡ወደ፡ባሕር፡ተወርወር፡ብትሉት፡ይኾናል፤
22፤አምናችኹም፡በጸሎት፡የምትለምኑትን፡ዅሉ፡ትቀበላላችኹ፡አላቸው።
23፤ወደ፡መቅደስም፡ገብቶ፡ሲያስተምር፡የካህናት፡አለቃዎችና፡የሕዝብ፡ሽማግሌዎች፡ወደ፡ርሱ፡
ቀረቡና፦በምን፡ሥልጣን፡እነዚህን፡ታደርጋለኽ፧ይህንስ፡ሥልጣን፡ማን፡ሰጠኽ፧አሉት።
24፤ኢየሱስም፡መልሶ፦እኔ፡ደግሞ፡አንዲት፡ነገር፡እጠይቃችዃለኹ፤እናንተም፡ያችን፡ብትነግሩኝ፡እኔ፡
ደግሞ፡እነዚህን፡በምን፡ሥልጣን፡እንዳደርግ፡እነግራችዃለኹ፤
25፤የዮሐንስ፡ጥምቀት፡ከወዴት፡ነበረች፧ከሰማይን፡ወይስ፡ከሰው፧አላቸው።እነርሱም፡ርስ፡በርሳቸው፡
ሲነጋገሩ፦ከሰማይ፡ብንል፦እንኪያስ፡ስለ፡ምን፡አላመናችኹበትም፧ይለናል፤
26፤ከሰው፡ግን፡ብንል፥ዮሐንስን፡ዅሉም፡እንደ፡ነቢይ፡ያዩታልና፥ሕዝቡን፡እንፈራለን፡አሉ።
27፤ለኢየሱስም፡መልሰው፦አናውቅም፡አሉት።ርሱም፡ደግሞ፦እኔም፡በምን፡ሥልጣን፡እነዚህን፡እንዳደርግ፡
አልነግራችኹም፡አላቸው።
28፤ነገር፡ግን፥ምን፡ይመስላችዃል፧አንድ፡ሰው፡ኹለት፡ልጆች፡ነበሩት፤ወደ፡አንደኛው፡ቀርቦ፦ልጄ፡
ሆይ፥ዛሬ፡ኺድና፡በወይኔ፡አትክልት፡ሥራ፡አለው።
29፤ርሱም፡መልሶ፦አልወድም፡አለ፤ዃላ፡ግን፡ተጸጸተና፡ኼደ።
30፤ወደ፡ኹለተኛውም፡ቀርቦ፡እንዲሁ፡አለው፡ርሱም፡መልሶ፦ዕሺ፡ጌታዬ፡አለ፤ነገር፡ግን፥አልኼደም።
31፤ከኹለቱ፡የአባቱን፡ፈቃድ፡ያደረገ፡ማን፡ነው፧ፊተኛው፡አሉት።ኢየሱስ፡እንዲህ፡አላቸው፦እውነት፡
እላችዃለኹ፥ቀራጮችና፡ጋለሞታዎች፡ወደእግዚአብሔር፡መንግሥት፡በመግባት፡ይቀድሟችዃል።
32፤ዮሐንስ፡በጽድቅ፡መንገድ፡መጥቶላችኹ፡ነበርና፥አላመናችኹበትም፤ቀራጮችና፡ጋለሞታዎች፡ግን፡
አመኑበት፤እናንተም፡ይህን፡አይታችኹ፡ታምኑበት፡ዘንድ፡በዃላ፡ንስሓ፡አልገባችኹም።
33፤ሌላ፡ምሳሌ፡ስሙ።የወይን፡አትክልት፡የተከለ፡ባለቤት፡ሰው፡ነበረ፤ቅጥርም፡ቀጠረለት፥መጥመቂያም፡
ማሰለት፥ግንብም፡ሠራና፡ለገበሬዎች፡አከራይቶ፡ወደ፡ሌላ፡አገር፡ኼደ።
34፤የሚያፈራበትም፡ጊዜ፡ሲቀርብ፥ፍሬውን፡ሊቀበሉ፡ባሮቹን፡ወደ፡ገበሬዎች፡ላከ።
35፤ገበሬዎቹም፡ባሮቹን፡ይዘው፡አንዱን፡ደበደቡት፡አንዱንም፡ገደሉት፡ሌላውንም፡ወገሩት።
36፤ደግሞ፡ከፊተኛዎች፡የሚበዙ፡ሌላዎች፡ባሪያዎችን፡ላከ፥እንዲሁም፡አደረጉባቸው።
37፤በዃላ፡ግን፦ልጄንስ፡ያፍሩታል፡ብሎ፡ልጁን፡ላከባቸው።
38፤ገበሬዎቹ፡ግን፡ልጁን፡ባዩ፡ጊዜ፡ርስ፡በርሳቸው፦ወራሹ፡ይህ፡ነው፤ኑ፥እንግደለውና፡ርስቱን፡
እናግኝ፡ተባባሉ።
39፤ይዘውም፡ከወይኑ፡አትክልት፡አወጡና፡ገደሉት።
40፤እንግዲህ፡የወይኑ፡አትክልት፡ጌታ፡በሚመጣ፡ጊዜ፡በእነዚህ፡ገበሬዎች፡ምን፡ያደርግባቸዋል፧
41፤እነርሱም፦ክፉዎችን፡በክፉ፡ያጠፋቸዋል፥የወይኑንም፡አትክልት፡ፍሬውን፡በየጊዜው፡ለሚያስረክቡ፡
ለሌላዎች፡ገበሬዎች፡ይሰጠዋል፡አሉት።
42፤ኢየሱስ፡እንዲህ፡አላቸው፦ግንበኛዎች፡የናቁት፡ድንጋይ፡ርሱ፡የማእዘን፡ራስ፡ኾነ፤ይህም፡ከጌታ፡
ዘንድ፡ኾነ፥ለዐይኖቻችንም፡ድንቅ፡ነው፡የሚለውን፡ከቶ፡በመጽሐፍ፡አላነበባችኹምን፧
43፤ስለዚህ፥እላችዃለኹ፥የእግዚአብሔር፡መንግሥት፡ከእናንተ፡ትወሰዳለች፥ፍሬዋንም፡ለሚያደርግ፡ሕዝብ፡
ትሰጣለች።
44፤በዚህም፡ድንጋይ፡ላይ፡የሚወድቅ፡ይቀጠቀጣል፤ድንጋዩ፡ግን፡የሚወድቅበትን፡ዅሉ፡ይፈጨዋል።
45፤የካህናት፡አለቃዎችና፡ፈሪሳውያንም፡ምሳሌዎቹን፡ሰምተው፡ስለ፡እነርሱ፡እንደ፡ተናገረ፡አስተዋሉ፤
46፤ሊይዙትም፡ሲፈልጉት፡ሳሉ፡ሕዝቡ፡እንደ፡ነቢይ፡ስላዩት፡ፈሯቸው።
== '''ምዕራፍ ፳፪''' ==