ከ«አዛኒያ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
 
መስመር፡ 2፦
'''አዛኒያ''' ([[ግሪክኛ]]፦ Ἀζανία) በታሪካዊ ምንጮች ውስጥ በምሥራቅ-ደቡባዊ [[አፍሪካ]] የተገኘ አገር ነበር።<ref name=":0">{{Cite journal|url = |title = Amalgamating eastern Gondwana: The evolution of the Circum-Indian Orogens|last = Collins & Pisarevsky|first = |date = 2004|journal = Earth-Science Reviews|doi = |pmid = |access-date = }}</ref> በ[[ሮሜ መንግሥት]] ዘመንና ምናልባት ከዚያም በፊት፣ ከ[[ሶማሊያ]]ና [[ኬንያ]] ጀምሮ<ref>Richard Pankhurst, ''An Introduction to the Economic History of Ethiopia'', (Lalibela House: 1961), p.21</ref> እስከ [[ታንዛኒያ]] ድረስ ያለው [[የሕንድ ውቅያኖስ]] ዳርቻ አገር ሁሉ «አዛኒያ» ተብሎ ነበር። [[የባንቱ ፍልሰት]] እዚያ ከደረሰ በፊት በተለይ የ[[ኩሻዊ ቋንቋ]] ተናጋሪዎች ይገኙበት ነበር።<ref name="Reference">https://scholar.lib.vt.edu/ejournals/ElAnt/V1N5/hilton.html</ref>
 
«የቀይ ባሕር ጉዞ መዝገብ» በ50 ዓም ግድም በግሪክ ተጽፎ ስለ አዛኒያ ይገልጻል። ከአፍሪቃ ቀንድ እስከ [[ራፕታ]] ወደብ ድረስ (በአሁን ታንዛኒያ) ይዘርጋል፤ ይህም ራፕታ የአዛኒያ ደቡባዊ ጫፍና መርካቶ ይባላል።<ref>[[George Wynn Brereton Huntingford]], ''The Periplus of the Erythraean Sea'', (Hakluyt Society: 1980), p.29</ref> በዚህ[[የዝሆን ጥርስ]]ና የ[[ኤሊ]] ቅርፊት በራፕታ ወደብ በንግድ እንደ ተገኙ ይላል። በዚህም ጽሑፍ ዘንድ የአዛኒያ ባህር ዳር እስከ አሁኑ [[ሞዛምቢክ]] ድረስ ለ[[ሒምያር]] (የመን) ንጉሥ [[ካሪብ ኢል]] ተገዥ ነበር።
 
[[ትልቁ ፕሊኒ]] እንደ ጻፈ፣ «የአዛኒያ ባሕር» (N.H. 6.34) ከ[[አዱሊስ]] መርካቶ (በአሁኑ [[ኤርትራ]]) ጀምሮ፤ ከዚያም [[የአፍሪካ ቀንድ]]ን ዞሮ ወደ ደቡብ ይገኝ ነበር። ከፕሊኒ በኋላ [[ክላውዲዎስ ቶለሚ]] (150 ዓም ግድም) እና [[ኮስማስ ኢንዲኮፕሌውስቴስ]] (550 ዓም) ደግሞ ጠቅሰውታል።.ኮስማስ እንዳለ በዘመኑ ለ[[አክሱም መንግሥት]] ተገዥ ነበር፤ [[ጥጃ]] በወርቅ እዚያ ይገዛል ይላል።