ከ«ኡሩካጊና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 6፦
 
አልፎ አልፎ ኡሩካጊና ከጎረቤት ከተሞቹ ጋር ተዋግቶ በመጨረሻ ግን ለ[[ኡሩክ]] ድል ሆነ። በዚህ ወቅት (2095 ዓክልበ. ግ.) ኡሩክ፣ ላጋሽና ሌሎቹ ከተሞች ሁሉ ለ[[ኡማ]] ገዢ ለ[[ሉጋል-ዛገ-ሲ]] ግዛት ተጨመሩ፤ ይህም በሱመር ሁሉ የገዛ መንግሥት ሆነ።
 
==የኡሩካግና ማሻሻሎች በላጋሽ የሚተርክ ሰነድ==
 
::«ቀድሞ ከጥንት ቡቃያዎች ጀምሮ የ[[መርከብ]] ኃላፊ መርከብን ይወስድ ነበር፤ የ[[አህያ]] መንጋ ኃላፊ አህያን ይወስድ ነበር፤ የ[[በግ]] መንጋ ኃላፊ በግን ይወስድ ነበር፤ የ[[አሣ]] ኃላፊ [አሣ]ን ይወስድ ነበር። ቄሶቹ የ[[ገብስ]] ቀለብ ይመዝኑ ነበር፤ የ[[ሱፍ]] እረኞች ለነጭ በግ በ[[ብር (ብረታብረት)|ብር]] ይከፍሉ ነበር፤ የመሬት ቀያሽ፣ የአዝማሪዎች አለቃ፣ አስተዳዳሪ፣ ጠማቂና ካቦዎች ሁሉ፣ ለመሥዋዕት በግ በብር ይከፍሉ ነበር። የአማልክት በሬዎች የገዢውን እርሻ ያርሱ ነበር፤ የገዢውም ሰብልና [[ኪያር]] በአማልክት እርሻ ይገኝ ነበር። ምርት የሆኑት አህዮችና በሬዎች ለቤተ መቅደስ አስተዳዳሪዎች ይታሥሩ ነበር፤ የገዢው ቅጥረኞች ግን የቤተ መቅደስ አስተዳዳሪዎች ገብስ ነበራቸው፤ የቤተ መቅደስ አስተዳዳሪዎችም ይገብሩ ነበር። አስተዳዳሪው በተራ ሰው እርሻ ላይ ዛፍ ሊያቋርጥ ወይም ፍሬውን ሊወስድ ይችል ነበር። ሬሳ በመቃብር ሲገባ፣ የመቃብር አለቃ ለራሱ 7 ጋን [[ቢራ]]፣ 420 [[ዳቦ]]ዎች፣ ግማሽ ''[[ጉር]]'' [3 ሊተር ያህል] ገብስ፣ አንድ ካባ ልብስ፣ አንድ ምጥምጥምና አንድ አልጋ ይወስድ ነበር፤ አገልጋዩም አንድ ሩብ ጉር ገብስ ይወስድ ነበር። ... ባለ እጅ ጥበበኛም ለዳቦ ለምኖ በእጁ ይቀብለው ነበር፤ የሠራተኞች ጥንድ የከተማ በር ኬላ ግብር ለራሳቸው ይወስዱ ነበር። የገዢው መኖርያ በገዢው እርሻ አጠገብ፣ የባለቤቱም መኖርያ በርስዋ እርሻ አጠገብ፣ የልጆቹም መኖርያዎች በርስሾቻቸው አጠገብ ይገኙ ነበር። ከጠረፎቹ እስከ ባሕሩ ድረስ ባለሥልጣናት ይገኙ ነበር። የቀድሞ አስተዳደር እንዲህ ነበር።
 
::«ጣኦቱ ኒንጊርሱ ከ36 ሺህ ሰዎች ለቅሞ የላጋሽ ገዢነቱን ለኡሩካግና በሰጠበት ጊዜ፣ ጥንታዊ ልማዶቹን ቀየረ። የመርከብ ኃላፊውን ከመርከቦች አስወገደ፤ የመንጋ ኃላፊውንም ከአህዮችና ከበጎች አስወገደ፤ የአሣ ኃላፊውንም ከአሦች አስወገደ። የእህል ቤት ኃላፊውን ከቄሶች ገብስ ቀለብ አስወገደ። ባለሥልጣናትን ከነጭ በግና ከመሥዋዕት በግ ብር ክፍያ አስወገደ፤ የቤተ መቅደስ አስተዳዳሪዎቹንም ግብር የሚቀበለው ባለሥልጣን አስወገደ። የገዢው፣ የባለቤቱም፣ የልጆቹም መንርያዎችና እርሾች ለጣኦታት ተመለሱ። ማንም ከጠረፎች እስከ ባሕር ድረስ ባለሥልጣን አይሆንም። ሬሳ ወደ መቃብር ለማስገባት፣ የመቃብር አለቃ 3 ጋን ቢራ፣ 80 ዳቦዎች፣ አንድ አልጋና አንድ ጥምጥም ይወስዳል፤ አገልጋዩም 1/8 ጉር ገብስ ይወስዳል። በጣኦቱ ዱር ውስጥቢሆን የመቃብር አለቃ 4 ጋን ቢራ፣ 240 ዳቦዎችና አንድ ሩብ ጉር ገብስ ይወስዳል፤ አገልጋዩም 1/8 ጉር ገብስ ይወስዳል። ሴት ቀስዮዋም አንድ ጥምጥምና መልካም ሽቶ ትወስዳለች። የጊርሱ አዝማሪዎች ቀለብ 420 [[ስንዴ]] ዳቦዎች ለአቀራረቡ፣ 40 ሙቅ ዳቦዎች ለመብላት፣ 10 ሙቅ ዳቦዎች ለገበታው፣ 5 ዳቦዎች ለ[...]፣ ሁለት ማሰሮና አንድ ጋን ቢራ ይሆናል። የላጋሽ አዝማሪዎች ቀለብ 490 ዳቦዎች፣ 2 ማሰሮና 1 ጋን ቢራ ይሆናል። የሌሎች አዝማሪዎች ቀለብ 406 ዳቦዎች፣ 1 ማሰሮና 1 ጋን ቢራ ይሆናል፤ የሽማግሌዎች ቀለብ 250 ዳቦዎች፣ 1 ማሰሮ ቢራ ይሆናል፤ የጣኦት ሽማግሌዎች ቀለብ 180 ዳቦዎች፣ 1 ማሰሮ ቢራ ይሆናል። ለዕውሩ አገልጋይ አንድ ለመብላት፣ 5 ለዳቦ፣ [...] 1 ለእኩለ ቀን ዳቦ፣ 6 ለእኩለ ሌሊት ዳቦ። የጣኦታት ሐውልቶች ኃላፊ ቀለብ 60 ዳቦዎች፣ 1 ማሰሮ ቢራና 1/4 ጉር ገብስ ይሆናል። የከተማ በር ኬላ ግብር ሠራተኞች ጥንድ ተሠረዘ። የቤተ መቅደስ አስተዳዳሪዎች በተራ ሰው እርሻ ላይ አይዘርፉም። ጥሩ አህያ ለአገልጋይ ቢወለድ፣ ጌታውም፦ «ካንተ እገዛለሁ» ቢለው፣ አገልጋዩም መልሶ «የምፈልገውን ብር ዋጋ ብትከፍለኝ» ቢለው፣ ካልገዛው በቁጣ አገልጋዩን አይመታም። የአገልጋይ ቤት ከጌታው ቤት አጠገብ ከሆነ፣ ጌታውም፦ «ካንተ እገዛለሁ» ቢለው፣ አገልጋዩም መልሶ «የምፈልገውን ብርና ገብስ ዋጋ ብትከፍለኝ» ቢለው፣ ካልገዛው በቁጣ አገልጋዩን አይመታም። እንዲህ አዋጀ ኡሩካግና። የላጋሽን ዜጎች ከዕዳ አወጣ፤ ወይም [...] በስርቆት ወይም በግዲያ ሲከሰሱ ወይም [...] ለዚህም ጉዳይ መፍትሄ መሠረተ። ድሃ አደግና ባልዋ ያረፈባት ለኃይለኞቹ አልተሰጡም። ...»
 
 
 
{{S-start}}