ከ«ሻውሽታታር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «500px|thumb 350px|thumb|የሻውሽታታር ማኅተም '''ሻውሽ...»
(No difference)

እትም በ14:51, 4 ጃንዩዌሪ 2019

ሻውሽታታርፓርሻታታር (ወይም ባራታርና) ቀጥሎ በሑራውያን ላይ የነገሡት የሚታኒ መሣፍንት ንጉሥ ነበር። ዘመኑ ምናልባት 1457-1417 ዓክልበ. ያሕል ነበር።

የሻውሽታታር ማኅተም

ኑዚ በተገኘ ሰነድ፣ የሚታኒ ንጉሥ ፓርሻታታር ወይም ፓርሻታር ባረፈበት ዓመት እንደ ተጻፈ፣ ሻውሽታታርም እንደ ተከተለው ይላል። በብዙዎች አስተሳሰብ ይህ ፓርሻታር እና ባራታርና (ፓራታርና) አንድ ንጉሥ ነበሩ። ሌሎች ግን የተለያዩ ነገሥታት ነበሩና ባራታርና ከፓርሻታታር ቀደመው የሚሉ ናቸው።

በሻውሽታታር መንግሥት ግዛት ውስጥ የሚከተሉት ነገሥታት ለርሱ ተገዥ ነበሩ፦ የአራፕኻ ንጉሥ ኢቅቲ-ተሹቡ፣ የሙኪሽ (አላላኽ) ንጉሥ ንፕመቃ፣ የኪዙዋትና ንጉሥ ሱናሱራ።

ግብጽ ፈርዖን 3 ቱትሞስ ዘመቻዎች በተለይ በ1453 ዓክልበ. ከሐለብ ስሜን የሚታኒን ሥራዊት በአርዓና አሸነፈ። በ1446 ዓክልበ. ቱትሞስ ፫ የሚታኒ አምባዎች በቃዴስ ዙርያ አጠፋ።

ከመቶ አመት በኋላ በሚታኒ የነገሠው ሻቲዋዛኬጥያውያን መንግሥት ንጉሥ ሱፒሉሊዩማ ጋር ባደረገው ውል፣ ሻውሽታታር አሦርን ዘርፎ የአሦር ቤተመንግሥት ወርቃም በሮችን ወደ ሚታኒ ዋና ከተማ ዋሹካኒ ወሰዳቸው ይላል። ይህ ምናልባት 1 አሹር-ናዲን-አሔ የአሦር ንጉሥ ሲሆን (1441 ዓግልበ) ከዚያ እስከ 1366 ዓክልበ. ድረስ የአሦር ነገሥታት ደግሞ ለሚታኒ ግዛት ተገዥ ሆኑ።

የቱትሞስ ተከታይ 2 አመንሆተፕ ደግሞ በሚታኒ ሥራዊት ላይ በሶርያ በ1433 እና በ1429 ዓክልበ. ይዘምት ነበር፤ በ1427 ዓክልበ. ከግብጽና ከሚታኒ ጋር ስምምነት ተደረገ።

የሻውሽታታር ተከታይ 1 አርታታማ እንደ ሆነ ይታስባል።