ከ«መለስ ዜናዊ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Tags: Replaced በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
የ197.156.103.251ን ለውጦች ወደ 196.188.192.12 እትም መለሰ።
Tag: Rollback
መስመር፡ 1፦
{{የፖለቲካ ሰው መረጃ
መለስ ሌባ ሰው ነው። ምንም ታሪክ የሌለው ሌባ።
| ስም = መለስ ዜናዊ
| ስዕል = Meles Zenawi.jpg
| የስዕል_መግለጫ =
| ቢሮ = [[የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር]]
| ቀናት = ከነሐሴ ፲፯ ቀን ፲፱፻፹፯ ዓ.ም. እስከ ነሐሴ ፲፬ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም.
| ፕሬዝዳንት = [[ነጋሶ ጊዳዳ]] <br/> [[ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ|መ/አለቃ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ]]
| ቀዳሚ = [[ታምራት ላይኔ]] ''(ተግባራዊ)''
| ተከታይ = [[ኃይለማሪያም ደሳለኝ]]
| ቢሮ2 = [[የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት]]
| ቀናት2 = ከግንቦት ፳ ቀን ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. እስከ ነሐሴ ፲፮ ቀን ፲፱፻፹፯ ዓ.ም.
| ጠቅላይ_ሚኒስትር2 = [[ተስፋዬ ዲንካ]] <br/> [[ታምራት ላይኔ]]
| ቀዳሚ2 = [[ተስፋዬ ገብረ ኪዳን]] ''(ተግባራዊ)''
| ተከታይ2 = [[ነጋሶ ጊዳዳ]]
| ሌላ_ስም = ለገሠ ዜናዊ አስረስ (የትውልድ)
| የተወለዱት = ሚያዝያ ፴ ቀን ፲፱፻፵፯ ዓ.ም. <br /> [[አድዋ]]፣ [[ኢትዮጵያ]]
| የሞቱት = ነሐሴ ፲፬ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም. <br /> [[ብረስልስ]]፣ [[ቤልጅግ]]
| ዜግነት =
| ፓርቲ = [[ሕወሐት]]፣ [[ኢህአዴግ]]
| ባለቤት = [[አዜብ መስፍን]]
| ልጆች =
| ሀይማኖት = የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ክርስትና
| ፊርማ =
}}
'''መለሰ ዜናዊ''' (የትውልድ ስማቸው '''ለገሠ ዜናዊ አስረስ''') ([[ሚያዝያ ፴]] ቀን [[1947|፲፱፻፵፯]] ዓ/ም - [[ነሐሴ ፲፬]] ቀን [[፳፻፬]] ዓ/ም) የ[[ኢትዮጵያ]] የፖለቲካ ሰው ነበሩ። በ[[አድዋ]] [[ትግራይ]] የተወለዱ ሲሆን ከ[[1987|፲፱፻፹፯]] ዓ/ም አንስተው እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ በኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትር ሥልጣን በከፍተኛው የአመራር ቦታ ላይ ነበሩ። የ[[ኢህአዴግ]]ና የ[[ሕውሓት]] ሊቀመንበር በመሆን ኢህአዴግ ስልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ ቆይተዋል።
 
አቶ መለስ ዜናዊ አባታቸው (አቶ ዜናዊ አስረስ<ref>http://ethiopiazare.com/the-news-50/the-news/289-meles-father</ref>) የትግራይ ተወላጅ ሲሆኑ፣ በእናታቸው በኩል ደግሞ [[ኤርትራዊ]] ናቸው።
 
መለስ በታወቀው ጀነራል ዊንጌት 2ኛ ደረጃ ተምህርት ቤት የተማሩና ከአጼ አህለስላሴ የኮከብ ተማሪዎች ሽልማት የተሸለሙ፣ ከዛም ወደ በረሃ ወርደው በታጋይነት ከመሰለፍቸው በፊት፤ የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ሜዲካል ፋክልቲ ተማሪ ነበሩ።  ትግርኛ፣አማርኛና፡ እንግሊዝኛ አቀላጥፈው መናገር ይችላሉ።
 
መለስ ዜናዊ ስልጣን ላይ በነበሩባቸው ጊዜያት ለሀገራቸው ኢትዮጵያ ባደረጓቸው አስተዋፅኦዎች የኢትዮጵያ ባለውለታ ናቸው ይባላሉ፡፡ ኢትዮጵያም እንደ እርሳቸው ያለ መሪ አግኝታ እንደማታውቅ በሰፊው ይነገራል፡፡
 
== ወደ ስልጣን አመጣጥ ==
አቶ መለስ የሚመሩት ሕውሓት የኮሎኔል [[መንግስቱ ኅይለ ማርያም]]ን አምባገነናዊ መንግስት በትጥቅ ትግል ሲታገሉ ከነበሩ ድርጅቶች አንዱ ነበር። አቶ መለስ የ[[ሕወሓት]] አመራር ኮሚቴ መሪ ሆነው በ1971 ተመረጡ፤ ቀጥሎም በ1975 የድርጅቱ ማእከላዊ ኮሚቴ ሊቀመንበር ሆኑ። የ[[ደርግ]] መንግሥት ከወደቀም ጀምሮ የሕወሓትና የ[[ኢህአዴግ]] ሊቀ-መንበርም ሆነው አገልግለዋል። ኢህአዴግ የአራቱ ፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም የኦሮሞ ህዝቦች ዲሞከራሲያዊ ድርጅት፣ የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ውህደት ነው። ወደ ስልጣን ሲመጡ በጊዜው ላቋቋሙት ጊዜያዊ መንግስት ፕረዚዳንት ሆነው ካገለገሉ በሗላ 1985 ለመጀመሪያ ጊዜ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው ተመረጡ። በጊዜው የፕረዚደንትነቱን ቦታ የተረከቡት ዶ/ር [[ነጋሶ ጊዳዳ]] ናችው።
 
== የሽግግር መንግስታቸው ==
የአምባገነኑ የመንግስቱ ኃይለ ማርያም አስተዳደር እንደ ወደቀ አዲስ አበባን የተቆጣጠረው ኢአሓዴግ በሕዝብ ምርጫ ሳይሆን ብሔረሰቦችን መሰረት ባደረገ በጥቂት ግለሰቦች የሽግግር መንግሥቱ በመቋቋሙ አብዛኛውን ሕዝብና ምሁራንን በጣም አስቆጣ።
 
== የኢህአዴግ ደጋፊዎች ==
በወቅቱ በአምባ ገነኑ ደርግ ስር ተጨቁኖ ለነበረው ድሃ ኢትዮጵያዊ የኢህአደግ ወደ ስልጣን መምጣት ሌላ አማራጭ ስላልነበር የኢሕአዴግን መንግስት ሕዝቡ ለመቀበል ስለ ተገደደ በጊዜው ኢህአዴግ ይህ ነው የተባለ ተቃውሞ አልገጠመውም። በአንጻሩ ከጅምሩ በትጥቅ ትግል ኢሕአዴግን ሲረዱ የነበሩ የአረብና የምዕራባውያን መንግስታት ከጎንህ አለን በማለት በሁለት እግሩ አንዲቆም አስችለውታል።
 
ይሁን እንጂ እያደር ሲመጣ የአቶ መለሰ ዚናዊ መንግስት የታገለለትን ዓላማ ስቶ ዲሞክራሲን በማፈን የነጻ ፕሬስ አፈና በማካሄድና የብአዊ መብት ረገጣ ስላበዛ ብዙ የምዕራባዊያን ድጋፍና ከማጣቱም በላይ የብዙ ሺ ኢትዮጵያዊያን ለስደት ዳርጎአል። ሆኖም ዓለም አቀፉን ሽብርተኛ ለመታገል በሚል ሽንገላ ሱማሌን በመውረሩ ምክንያት በጆርጅ ቡሽ የምትመራ አሜሪካ ቀንደኛና ዋነኛ የኢህአዴግ ደጋፊ ሆና ቀርታለች። ቀጣዩ የአሜሪካ መሪ ባራክ ኦባማም የአገራቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ ካላቸው ፍላጎት አልቃይዳንና አልሸባብ የተባሉ የአክራሪ እስላም ቡድኖችን እየታገልኩ ነው ላለው ኢሕአዴግን ድጋፋቸውን ቀጥለዋል።
 
== የኢህአዴግ ተቃዋሚዎች ==
[[ስዕል:MelesZenawi1972.jpg|left|200px|thumb| መለስ ዜናዊ ከ[[አጼ ኃይለ ስላሴ]] ሽልማት እንደተቀበለ (1964 ዓ.ም.)]]
ምንም እንኳ በደርግ የግፍ አገዛዝ የተማረረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ኢህአዴግን ለመቀበልና አብሮ ለመስራት ወደ ኋላ ባይልም ውሎ ሲያድር ግን በኢህአዴግ የአገር ውስጥ ፖሊሲ መከፋቱ አልቀረም። የ[[ኦሮሞ ነጻነት ግንባር]] (ኦነግ) ብሎ ራሱን የስየመው ቡድን ከኢህአዴግ ጋር በመቃቃሩ ራሱን ከፓርላማውና ከካቢኔው አግልሎ ወደ ትጥቅ ትግሉ ተመለሰ።
 
ጠ.ሚ. መለስ የኤርትራን የመገንጠል ጥያቄ ያለምንም ማንገራገር መፍቀዳቸው ብቻ ሳይሆን ሁሉም ብሔረሰብ እንዲገነጠል የሚያስችለውን አንቀጽ በሕገ መንግስታቸው በማካተታቸው በተለይ በምሁራን ዘንድ የከረረ ተቃውሞ አስነስቶባቸዋል። ሁሉም በክልሉ በቋንቋው ይማር የተሰኘው ፖሊሲያቸውም በብዙዎች ዘንድ ጥርጣሬና መከፋፈልን በመፍጠሩ በሀገርና ከሀገር ውጭ በተደጋጋሚ የተቃውሞ ሰልፎች ተካሂዶባቸዋል።
 
በ1997 ዓ.ም. አጋማሽ ጠቅላላ ምርጫ ሲደረግ ከተለያዩ የፖለቲካ ህቡዕ ፓርቲዎች የተውጣጣ [[ቅንጅት]] የተሰኘ ጥምር የፖለቲካ ፓርቲ እንደ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ተወዳደረ። በውጤቱም የዓለም ታዛቢዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ ከተማ ከመቶ 97 እጁ መራጭ የተቃዋሚውን ፓርቲ ቅንጅትን መረጠ። በውጤቱ የተደናገጠው የአቶ መለስ መንግስት ለመጀመሪያ ጊዜ የአዲስ አበባን ፖሊስ በፌዴራል ቁጥጥር ስር አዞረ። የአዲስ አበባ ምክር ቤትንም በ[[ኦሮሚያ]] መስተዳደር ስር እንዲተዳደር አዲስ ድንጋጌ አወጣ።
 
ይሁን እንጂ ብዙም ገለልተኛ ታዛቢ በሌለበት ከአዲስ አበባ ውጪ [[ኢሕአዴግ]] 90 በመቶ ማሸነፉ ስለታወጀ ተቃዋሚዎች አድልዎ ተደርጎብናልና ምርጫው እንደገና ይጣራ ብለው ለከፍተኛ ፍርድ ቤት የክስ ማመልከቻ በማስገባታቸው ማጣሪያ ተካሄደ። ተቃዎሚዎች በጠቅላላው የምርጫ ውጤት ባለመስማማታቸው ያሸነፉበትን የፓርላማ ወንበር ባለመቀበል የገዢው ፓርቲ በበላይነት ከተቆጣጠረው ፓርላማ ራሳቸውን አገለሉ።
 
[[ሚሥስ አና ጎሜዝ]] የተባሉ የአውሮፓ ታዛቢ ቡድን መሪ ምርጫው አድልዎና ጫና እንደነበረበት ለዓለም ሕዝብ ምስክርነታቸውን ተናገሩ። አብዛኛዎቹ ታዛቢዎች ([[አፍሪካ ሕብረት]] አና የ[[ጂሚ ካርተር]]ማእከል) ምርጫው በኢትዮጲያ ከተካሄዱ ምርጫዎች በጣም የተሻለ መሆኑን መሰከሩ። በሺ የሚቆጠሩ የቅንጅት ደጋፊዎች በዋና ዋና ከተማዎች በመውጣት ሰላማዊ ሰልፍ በቁጣ በሚገልጹበት ጊዜ ቁጥሩ በርካታ የሆነ ሕዝብ በፖሊስ በቀጥታ በተተኮሰ ጥይት ሕይወቱን አጥቶአል። የአቶ መለስ መንግስት አብዛኛዎችን በህዝብ የተመረጡ የ[[ቅንጅት]] ፓርቲ አባላትንና በሺህ የሚቆጠሩ አባላትን ባገር ክህደት አና መንግስትን ለመገልበጥ በመሞከር ከሰሳቸው። ሁለት ዓመት በፈጀ የፍርድ ሂደትም ፍርድ ቤቱ የቅንጅት መሪዎችን አገርን በመክዳት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው አገኛቸው። ይሁን እንጂ ሁሉም የ [[ቅንጅት]] መሪዎችና አብዛኛው ደጋፊ አባላት ጥፋታቸውን አምነው ይቅርታ በመጠየቃቸው ከእስር ነጻ ወጡ።
 
{{Template:EthiopianPMs}}
 
[[መደብ:የኢትዮጵያ መሪዎች]]