ከ«ባራታርና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
 
መስመር፡ 1፦
'''ባራታርና''' እንደሚታመን ከ[[1 ሹታርና]] ቀጥሎ በ[[ሑራውያን]] ላይ የነገሡት የ[[ሚታኒ]] መሣፍንት ንጉሥ ነበር። እንዲህ ከሆነ ዘመኑ ምናልባት 1480-57 ዓክልበ. ያሕል ነበር።
 
ስሙ በተለይ የሚታወቀው በ[[አላላኽ]] ([[ሙኪሽ]] አገር) ንጉሥ [[ኢድሪሚ]]ና በ[[ኪዙዋትና]] ንጉሥ [[ፒሊያ]] መካከል በተደረገው ስምምነት ውል ውስጥ እንዲሁም በ[[ኢድሪሚ ሐውልት]] ላይ ሲታይ ነው። በዚህ መሠረት ባራታርና ንጉሥ ሲሆን የ[[ያምኻድ]]ን ቅሬታ በ[[ሐለብ]] ያዘ፣ የሐለብም አልጋ ወራሽ ኢድሪሚ ወደ [[ሐቢሩ]] ወገን ሸሽቶ ከሰባት ዓመት ስደት በኋላ በርዳታቸው በኩል አላላኽን ለመያዝ ቻለ። ሆኖም አላላኽ ለባራታርና ተገዥ እንዲሆን እንደ ፈቀደ ይጠቀሳል። የባራታርና አርእስት «የሑራውያን ሥራዊት ንጉሥ» ተብሏል። የባራታርና ግዛት ወደ ምሥራቅ እስከ [[ኑዚ]]ና እስከ [[አራፕኻ]] ድረስ እንደ ዘረጋ ይባላል።
 
በኑዚ በተገኘ ሰነድ፣ የሚታኒ ንጉሥ [[ፓርሻታታር]] (ወይም ፓርሻታር) ባረፈበት ዓመት እንደ ተጻፈ፣ [[ሻውሽታታር]]ም እንደ ተከተለው ይላል። በብዙዎች አስተሳሰብ ይህ ፓርሻታር እና ባራታርና (ፓራታርና) አንድ ንጉሥ ነበሩ። ሌሎች ግን የተለያዩ ነገሥታት ነበሩና ባራታርና ከፓርሻታታር ቀደመው የሚሉ ናቸው።