ከ«ባራታርና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''ባራታርና''' እንደሚታመን ከ[[1 ሹታርና]] ቀጥሎ በ[[ሑራውያን]] ላይ የነገሡት የ[[ሚታኒ]] መሣፍንት ንጉሥ ነበር። እንዲህ ከሆነ ዘመኑ ምናልባት 1480-57 ዓክልበ. ያሕል ነበር።
 
ስሙ በተለይ የሚታወቀው በ[[አላላኽ]] ንጉሥ [[ኢድሪሚ]]ና በ[[ኪዙዋትና]] ንጉሥ [[ፒሊያ]] መካከል በተደረገው ስምምነት ውል ውስጥ እንዲሁም በ[[ኢድሪሚ ሐውልት]] ላይ ሲታይ ነው። በዚህ መሠረት ባራታርና ንጉሥ ሲሆን የ[[ያምኻድ]]ን ቅሬታ በ[[ሐለብ]] ያዘ፣ የሐለብም አልጋ ወራሽ ኢድሪሚ ወደ [[ሐቢሩ]] ወገን ሸሽቶ ከሰባት ዓመት ስደት በኋላ በርዳታቸው በኩል አላላኽን ለመያዝ ቻለ። ሆኖም በዚሁ ውል አላላኽ ለባራታርና ተገዥ እንዲሆን እንደ ፈቀደ ይጠቀሳል። የባራታርና አርእስት «የሑራውያን ሥራዊት ንጉሥ» ተብሏል። የባራታርና ግዛት ወደ ምሥራቅ እስከ [[ኑዚ]]ና እስከ [[አራፕኻ]] ድረስ እንደ ዘረጋ ይላል።ይባላል።
 
በኑዚ በተገኘ ሰነድ፣ የሚታኒ ንጉሥ [[ፓርሻታታር]] (ወይም ፓርሻታር) ባረፈበት ዓመት እንደ ተጻፈ፣ [[ሻውሽታታር]]ም እንደ ተከተለው ይላል። በብዙዎች አስተሳሰብ ይህ ፓርሻታር እና ባራታርና (ፓራታርና) አንድ ንጉሥ ነበሩ። ሌሎች ግን የተለያዩ ነገሥታት ነበሩና ባራታርና ከፓርሻታታር ቀደመው የሚሉ ናቸው።