ከ«ኢድሪሚ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «350px|thumb|የኢድሪሚ ሐውልት '''ኢድሪሚ''' ከ1473 እስከ 1443 ዓም ያህል ድረስ የ[[ሙኪሽ]...»
 
No edit summary
መስመር፡ 2፦
'''ኢድሪሚ''' ከ1473 እስከ 1443 ዓም ያህል ድረስ የ[[ሙኪሽ]] አገር ([[አላላኽ]] ከተማ) ንጉሥ ነበረ።
 
የኢድሪሚ ታሪክ በተለይ ከሐውልቱ [[አካድኛ]] ጽሑፍ የሚታወቀው ነው። የ[[ሐለብ]] መጨረሻ ንጉሥ የ[[1 ኢሊም-ኢሊማ]] ልጅ ነበር፣ ይህም ሥርወ መንግሥት ቀድሞ የ[[ያምኻድ]] መንግሥት ተብሎ ነበር። በ1480 ዓክልበ. ገደማ የ[[ሑራውያን]] ንጉሥ [[ባራታርና]] ሐለብን ወደ [[ሚታኒ]] መንግሥት እንደ ጨመረው ይታመናል። ኢድሪሚና ቤትሠቡ ከሐለብ ወደ [[ኤማር]] ሸሹ። ኢድሪሚ ከዚያ ወደ [[ከነዓን (ጥንታዊ አገር)|ከነዓን]] ምድር [[አሚያ]] ከተማ ሂዶ ከ[[ሐቢሩ]] ወገን ጋር ለሰባት ዓመት ቆየ ይላል። በዚያ በስደት ሆኖ ከሐቢሩና ሐገሩ ስደተኞች መካከል ሥራዊት ያሕል ሰበሰበ። በ1473 ዓክልበ እነርሱ በመርከብ በሶርያ ተመልሰው ደረሱ፣ አላላኽን ለመያዝ ቻሉና የአላላኽ፣ የ[[ኑሓሼ]]ና የ[[ኒያ]] ኗሪዎች ተደሰቱ፤ ሙኪሽ ከተባለው አገር ጋር ተባበሩ ይላል። ባራታርና ግን ለሰባት ዓመት ጠላቱ ሆነ። በመጨረሻ በ1465 ዓም አካባቢ ኢድሪሚ መልክተኛውን ወደ ባራታርና ልኮ «እኛ ዱሮ የሑራውያን ጓደኞች ነበርን» የሚልበሚል መልዕክት አሳሰበው። ባራታርና ይህን ተቀበለና ኢድሪሚ ለሚታኒ ጥገኛ ንጉሥ ሆኖ በሙኪሽ እንዲሆንእንዲቆይ ፈቀደ። [[ኪዙዋትና]] የተባለው አገር ደግሞ የሚታኒ ጥገኛ እንደ ተደረገ ይመስላል። ከዚህ በኋላ ኢድሪሚ በ[[ሐቲ]] ([[የኬጥያውያን መንግሥት]]) ላይ ዘምቶ ሰባት አምባዎች እንደያዘባቸው ይላል። ከዚያ ሕዝቡን በጸጥታ አስተዳደረው። ጸሓፊውም ሻሩዋ ኢድሪሚ ለ30 አመት እንደ ገዛ በማለት ጨመረ።
 
ለኢድሪሚ ሁለት ሌሎች ጽላቶች ይታወቃሉ። ከነዚህ አንዱ ከኢድሪሚና ከኪዙዋትና ንጉሥ [[ፒሊያ]] መካከል የተደረገው ውል ነው። በዚህ ውል መሠረት ከአንዱ አገር ወደ ሌላው የሸሹት ባርዮች እንዲመለሱ አስቻለ። ባርያውን የያዘው ሰው 500 [[ሰቀልlሰቀል]] [[መዳብ]] ለወንድ፣ 1000 ለሴት ባርያ እንዲከፈል አዘዘ። ወይም የባርያው ጌታ እራሱ ባርያውን ለመያዝ እርስ በርስ ወደ ኪዙዋትናም ሆነ ሙኪሽ መግባቱን በነጻ ፈቀደው።
 
ኢድሪሚ ብዙ ጣኦታት እንዳገለገለ ስለ ጻፈ በእርግጥ አረመኔ ንጉሥ ነበር። በከነዓን ውስጥ ቢቆይ [[ብሉይ ኪዳን]] ከ[[እስራኤል]] ውጭ በዚህ ለነገሡት አረመኔ ነገሥታት ብዙ ትኩረት አይሰጥም፤ ግን [[ጎቶንያል]] ፈራጃቸው የሆነበት ወቅት ያሕል ይመስላል። የግብጽ ፈርዖን [[3 ቱትሞስ]] ደግሞ በኢድርሚበኢድሪሚ ዘመን በ[[መጊዶ]]ና በሶርያ ይዘምት ነበር።
 
የኢድሪሚ ልጅ [[ኒፕመቃ]] በሙኪሽ ዙፋን ላይ ተከተለው።