ከ«ባራታርና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 3፦
ስሙ በተለይ የሚታወቀው በ[[አላላኽ]] ንጉሥ [[ኢድሪሚ]]ና በ[[ኪዙዋትና]] ንጉሥ [[ፒሊያ]] መካከል በተደረገው ስምምነት ውል ውስጥ ሲታይ ነው። በዚህ መሠረት ባራታርና ንጉሥ ሲሆን የ[[ያምኻድ]]ን ቅሬታ በ[[ሐለብ]] ያዘ፣ የሐለብም አልጋ ወራሽ ኢድሪሚ ወደ [[ሐቢሩ]] ወገን ሸሽቶ ከሰባት ዓመት ስደት በኋላ በርዳታቸው በኩል አላላኽን ለመያዝ ቻለ። ሆኖም በዚሁ ውል አላላኽ ለባራታርና ተገዥ እንዲሆን እንደ ፈቀደ ይጠቀሳል። የባራታርና አርእስት «የሑራውያን ሥራዊት ንጉሥ» ተብሏል። የባራታርና ግዛት ወደ ምሥራቅ እስከ [[ኑዚ]]ና እስከ [[አራፕኻ]] ድረስ እንደ ዘረጋ ይላል።
 
በኑዚ ደግሞበተገኘ ሰነድ፣ የሚታኒ ንጉሥ [[ፓርሻታታር]] (ወይም ፓርሻታር) ባረፈበት ዓመት እንደ ተጻፈ፣ [[ሻውሽታታር]]ም እንደ ተከተለው ይላል። በብዙዎች አስተሳሰብ ይህ ፓርሻታር እና ባራታርና (ፓራታርና) አንድ ንጉሥ ነበሩ። ሌሎች ግን የተለያዩ ነገሥታት ነበሩና ባራታርና ከፓርሻታታር ቀደመው የሚሉ ናቸው።
 
የ[[ግብጽ]] [[ፈርዖን]] [[3 ቱትሞስ]] [[የመጊዶ ውጊያ]] በ1465 ዓክልበ.ግ. ተዋግቶ በ«ናሓሪን» (ሚታኒ) ላይ ሲዘመት የሚታኒው ንጉሥ ስም ባይዘገብም በሰፊው በሚገኘው ዘመናዊ አስተያየት ዘንድ ይህ ዘመቻ የባራታርና (ወይስ የፓርሻታታር) ዘመን ውስጥ ሆኖ ነነር።