ከ«ካሣውያን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 31፦
በ1507 ዓክልበ. ([[ኡልትራ አጭር]]) [[የኬጥያውያን መንግሥት]] ንጉሥ [[1 ሙርሲሊ]] ከ[[ሐቲ]] አገር ([[አናቶሊያ]] እስከ ባቢሎን ድረስ ዘምቶ የባቢሎኒያ [[አሞራዊ]] መንግሥት አስጨረሰና የባቢሎን ዋና ጣዖት የ[[ማርዱክ]]ን ሐውልት ዘርፎ ወደ [[ሐቱሳሽ]] ተመለሰ። ከዚህ ማጥፋት በኋላ በመዝገቦች ጉድለት «የጨለመ ዘመን» ሊባል ይችላል። ከላይ የተጠቀሰው «አጉም-ካክሪሜ ጽላት» እንዳለ ከጊዜ በኋላ ካሣዊው ንጉሥ አጉም ካክሪሜ የማርዱክን ሐውልት ከ«ኻና አገር» አስመለሰው። «''የማርዱክ ትንቢት''» የተባለው ድርሰት ደግሞ ሐውልቱ በሐቲ አገር የቆየው ዘመን 24 አመት ነበር ሲል፣ ይህ ግን ከ1000 አመታት ያህል በኋላ በመጻፉ አጠያያቂ ይባላል።
 
የአጉም ልጅ [[ቡርና-ቡርያሽ]] 1480 ዓክልበ. ግድም ከ[[አሦር]] ንጉሥ [[3 ፑዙር-አሹር]] ጋር የደንበር ውል ተዋወለ፣ ከዚህ ዘመን ጀምሮ አሦርና ባቢሎን የመስጴጦምያ ዋና ኃያላት ሆኑ። ከባቢሎን ደቡብ በድሮው [[ሱመር]] የተገኘው ግዛት «[[የባሕር ምድር]]» እንዲሁም ለካሣውያንና ለቡርና-ቡርያሽ ልጅ [[ኡላም-ቡርያሽ]] በ1463 ዓክልበ. ያህል ወደቀ።
 
[[መደብ:የመስጴጦምያ ታሪክ]]