ከ«የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አንድ ለውጥ 350801 ከ2601:446:4400:1150:E0E9:C1C2:4AFF:30FF (ውይይት) ገለበጠ
Tag: Undo
መስመር፡ 15፦
:«እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘቧም ሁሉ የሰለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ [[ኢየሩሳሌም]] መጥቶ ነበር...»
 
በዚህ ንባብ ዘንድ ፊልጶስ ጃንደረባውን የትንቢተየ[[ትንቢተ ኢሳይያስ]] ክፍል እንዲገባው አስረድቶት በክርስትና አጠመቀው። ንግሥት[[ግርማዊት ህንደኬ ፯ኛ]] ከ፴፬ ዓ.ም. እስከ ፵፬ ዓ.ም. ገደማ በኢትዮጵያ የነገሡ ናቸው።
 
በ፬ኛው ምዕተ ዘመን በወንድማማቾቹ በ[[ንጉሥ ኤዛና]] እና በ[[ንጉሥ ሳይዛና]]ዘመን በ[[ፍሬምናጦስ]] አማካይነት ክርስትና የግዛቱ ይፋዊ ሃይማኖት ሆነ። ይህ ፍሬምናጦስ በኢትዮጵያ «አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን» ተብሎ ይታወቃል። በወጣትነት ዕድሜው ከአጎቱ ከፈላስፋው ከመሮፔዎስ እና ከወንድሙ ከ[[ሲድራኮስ]] ጋራ መርከባቸው ስለሰመጠች ከወንድሙ ጋር ከሞት ተርፈው ምጽዋ አጠገብ ተገኙ። ወደ ንጉሦቹም ግቢ አመጡዋቸውና ቀስ በቀስ ከፍተኛ ተጽእኖ ያለበት ደረጃ አገኙ። ንጉስ ኤዛና ደግሞ ወደ ክርስትና ለውጠው እንዲጠመቁ አደረጉ። ኤዛና ፍሬምናጦስን ለኢትዮጵያ አቡነ እንዲሾም ለመጠይቅ ወደ እስክንድርያ ላኩዋቸውና የእስክንድርያ ጳጳስ [[አትናቴዎስ]] ፍሬምናጦስን ሾሞ ላከው። ፍሬምናጦስ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ሲሆን የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ [[አቡነ ባስልዮስ]] ደግሞ ፻፲፩ኛው መሆናቸው ነው።