ከ«2 ቱትሞስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «{{የንጉሥ መረጃ | ስም = ቱትሞስ ዓኸፐረንሬ | ርዕስ = የግብጽ ፈርዖን | ስዕል=Stone bloc...»
(No difference)

እትም በ22:40, 25 ኖቬምበር 2018


፪ ቱትሞስ ዓኸፐረንሬ (ግብጽኛ፦ /ጀሁቲመስ/) በጥንታዊ ግብጽግብጽ አዲስ መንግሥትና የ18ኛው ሥርወ መንግሥት ፈርዖን ሲሆን ምናልባት 1501-1487 ዓክልበ. የገዛ ነበረ።

ቱትሞስ ዓኸፐረንሬ
የ፪ ቱትሞስ ስዕል በካርናክ ቤተመቅደስ
የ፪ ቱትሞስ ስዕል በካርናክ ቤተመቅደስ
የግብጽ ፈርዖን
ግዛት 1501-1487 ዓክልበ.
ቀዳሚ 1 ቱትሞስ
ተከታይ ሃትሸፕሱት
ባለቤት ሃትሸፕሱት፣ ኢሰት
ሥርወ-መንግሥት 18ኛው ሥርወ መንግሥት
አባት 1 ቱትሞስ

2 ቱትሞስ የቀዳሚው የ1 ቱትሞስና የንግሥቱ ሙትኖፍረት ልጅ ነበር። የ2 ቱትሞስ ዋና ንግሥት ደግሞ ያባቱና የሌላይቱ ንግሥት አሕሞስ ልጅ ነበረች። የ2 ቱትሞስ ቁባት ንግሥት ኢሰት ተባለች፣ እርሷም የተከታዩ 3 ቱትሞስ ሆነች።

ማኔጦን መሠረት ለ13-14 ዓመት እንደ ገዛ ባብዛኛው ይቀበላል። አንዳንድ መምህሮች ግን ዘመኑ ከ3-4 አመት በላይ አይሆንም ይላሉ።

በ፪ ቱትሞስ ዓኸፐረንሬ ዘመን አባቱ ከኩሽ መንግሥት የያዛቸው የኖቢያ ግዛቶች ያምጹበት ነበር፤ እሱ ግን ሥራዊቱን ልኮ አስመለሠው።

የጦር አለቃው አሕሞስ ፐን-ነኽበት ደግሞ «ሻሱ» በተባለ ወገን ላይ ዘምቶ በርካታ ምርከኞች እንደ ያዘ ይላል። እነኚህ በደቡብ ከነዓን የተገኙት የኤዶምያስ ሰዎች ወይም ሌሎች እንደሚሉ ዕብራውያን ነበሩ። በተጨማሪ ሌላ የተገኘ ጽሑፍ እንዳለን ዓኸፐረንሬ በረጨኑ (ሶርያ) እስከ ኒይ ከተማ ድረስ ዘመተ። ወደ ሶርያ የደረሱ በመርከብ ወይም በመሬት እንደ ደረሱ አልተገለጸም።

የ፪ ቱትሞስ ተከታይ በይፋ ልጁ ፫ ቱትሞስ ሲሆን እሱ ግን ገና ሕጻን ልጅ ሆኖ የቱትሞስ ንግሥት ሃትሸፕሱት ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴው፣ በቅርብም ጊዜ ውስጥ በራስዋ መብት ፈርዖን ተባለች። በ22ኛ ዓመትዋ (1466 ዓክልበ. ግ.) ዓርፋ ያንጊዜ ፫ ቱትሞስ ለብቻው ፈርዖን ሆነ።

ቀዳሚው
1 ቱትሞስ
ግብፅ ፈርዖን
1501-1483 ዓክልበ.
ተከታይ
ሃትሸፕሱት