ከ«ዜቡል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
 
መስመር፡ 6፦
የተዘገቡለት ድርጊቶች ጥቂት ናቸው። መጀመርያው ለቄኔዝ ሦስት ሴት ልጆች ሰፊ ርስቶች አካፈለላቸው። ዜቡልም ለ[[ያህዌ]] አንድ ግምጃ ቤት አቁሞ 20 መክሊት [[ወርቅ]]ና 250 መክሊት [[ብር (ብረታብረት)|ብር]] ከሕዝቡ ተቀበለ። የጣኦታት ወርቅ ወይም ብር ግን አይቀብልም ነበር።
 
የዕረፍቱ ጊዜ ሲቅርብሲቀርብ ለሕዝቡ እንዲህ ብሎ ተናገረ፦ «ከኛ ቀድሞ የሆኑት ሰዎች የመሠክሩትን ምስክሮች ተመልከቱ። ልባችሁ እንደ ባሕሩ ማዕበል አይሁን፤ ነገር ግን የባሕሩ ማዕበል በባሕሩ ውስጥ ካለው በቀር እንደማያውቅ፣ እንዲህ ልባችሁ በሕግ ቅዱስ ውስጥ ካለው በቀር በምንም አያስብ።»
 
ከዚህም በኋላ እስራኤላውያን በ[[እግዚአብሔር]] ፊት እንደገና ክፉ ሆኑና በ[[ሓጾር]] ንጉሥ [[ኢያቢስ]] ስር ለ20 ዓመታት ተገዙ። ስለዚህ፣ ይህ ሰነድ በመጽሐፈ መሳፍንት የተጠቀሱትን የ[[ኲሰርሰቴም]] (8 አመታት)፣ የጎቶንያል (40 ዓመታት)፣ የ[[ዔግሎም]] (18 ዓመታት)፣ እና የ[[ናዖድ]] (80 ዓመታት) ዘመናትን ይዘልላል። በመጽሐፈ መሳፍንት የኲሰርሰቴም ዘመን ኢያሱ ካረፈ በኋላ ባልተወሰነ ጊዜ ሆነ። ስለዚህ ስለ ቄኔዝና ዜቡል ዘመኖች ያለው ትዝታ ትክክል ከሆነ፣ እነዚህ 82 ዓመታት ከኢያሱ በኋላ እና ከኲሰርሰቴም በፊት (1587-1505 ዓክልበ.) መሰካት ነበረባቸው።