ከ«ቅዱስ ጴጥሮስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ
መስመር፡ 129፦
22፤ርሱም፡መላእክትና፡ሥልጣናት፡ኀይላትም፡ከተገዙለት፡በዃላ፡ወደ፡ሰማይ፡ኼዶ፡በእግዚአብሔር፡ቀኝ፡አለ።
==ምዕራፍ ፬==

1-2፤ክርስቶስም፡በሥጋ፡ስለ፡እኛ፡መከራን፡ስለተቀበለ፥ከእንግዲህ፡ወዲህ፡በሥጋ፡ልትኖሩ፡በቀረላችኹ፡
ዘመን፡እንደእግዚአብሔር፡ፈቃድ፡እንጂ፡እንደ፡ሰው፡ምኞት፡እንዳትኖሩ፥እናንተ፡ደግሞ፡ያን፡ዐሳብ፡እንደ፡
ዕቃ፡ጦር፡አድርጋችኹ፡ያዙት፥በሥጋ፡መከራን፡የተቀበለ፡ኀጢአትን፡ትቷልና።
3፤የአሕዛብን፡ፈቃድ፡ያደረጋችኹበት፡በመዳራትና፡በሥጋ፡ምኞትም፡በስካርም፡በዘፈንም፡ያለልክም፡
በመጠጣት፡ነውርም፡ባለበት፡በጣዖት፡ማምለክ፡የተመላለሳችኹበት፡ያለፈው፡ዘመን፡ይበቃልና።
4፤በዚህም፡ነገር፡ወደዚያ፡መዳራት፡ብዛት፡ከነርሱ፡ጋራ፡ስለማትሮጡ፡እየተሳደቡ፡ይደነቃሉ፤
5፤ግን፡እነርሱ፡በሕያዋንና፡በሙታን፡ላይ፡ሊፈርድ፡ለተዘጋጀው፡መልስ፡ይሰጣሉ።
6፤እንደሰዎች፡በሥጋ፡እንዲፈረድባቸው፡በመንፈስ፡ግን፡እንደ፡እግዚአብሔር፡እንዲኖሩ፡ስለዚህ፡ምክንያት፡
ወንጌል፡ለሙታን፡ደግሞ፡ተሰብኮላቸው፡ነበርና።
7፤ዳሩ፡ግን፡የነገር፡ዅሉ፡መጨረሻ፡ቀርቧል።እንግዲህ፡እንደ፡ባላእምሮ፡ዐስቡ፥
8፤ትጸልዩም፡ዘንድ፡በመጠን፡ኑሩ፤ፍቅር፡የኀጢአትን፡ብዛት፡ይሸፍናልና፥ከዅሉ፡በፊት፡ርስ፡በርሳችኹ፡
አጥብቃችኹ፡ተዋደዱ።
9፤ያለማንጐራጐር፡ርስ፡በርሳችኹ፡እንግድነትን፡ተቀባበሉ፤
10፤ልዩ፡ልዩን፡የእግዚአብሔርን፡ጸጋ፡ደጋግ፡መጋቢዎች፡እንደ፡መኾናችኹ፥እያንዳንዳችኹ፡የጸጋን፡ስጦታ፡እንደተቀበላችኹ፡መጠን፡በዚያው፡ጸጋ፡ርስ፡በርሳችኹ፡አገልግሉ፤11፤ማንም፡ሰው፡የሚናገር፡ቢኾን፥እንደእግዚአብሔር፡ቃል፡ይናገር፤የሚያገለግልም፡ቢኾን፥እግዚአብሔር፡
በሚሰጠኝ፡ኀይል፡ነው፡ብሎ፡ያገልግል፤ክብርና፡ሥልጣን፡እስከ፡ዘለዓለም፡ድረስ፡ለርሱ፡በሚኾነው፡
በኢየሱስ፡ክርስቶስ፡በኩል፡እግዚአብሔር፡በነገር፡ዅሉ፡ይከብር፡ዘንድ፤አሜን።
12፤ወዳጆች፡ሆይ፥በእናንተ፡መካከል፡እንደ፡እሳት፡ሊፈትናችኹ፡ስለሚኾነው፡መከራ፡ድንቅ፡ነገር፡እንደ፡
መጣባችኹ፡አትደነቁ፤
13፤ነገር፡ግን፥ክብሩ፡ሲገለጥ፡ደግሞ፡ሐሤት፡እያደረጋችኹ፡ደስ፡እንዲላችኹ፥በክርስቶስ፡መከራ፡
በምትካፈሉበት፡ልክ፡ደስ፡ይበላችኹ።
14፤ስለክርስቶስ፡ስም፡ብትነቀፉ፡የክብር፡መንፈስ፡የእግዚአብሔር፡መንፈስ፡በእናንተ፡ላይ፡ያርፋልና፥ብፁዓን፡ናችኹ።
15፤ከእናንተ፡ማንም፡ነፍሰ፡ገዳይ፡ወይም፡ሌባ፡ወይም፡ክፉ፡አድራጊ፡እንደሚኾን፡ወይም፡በሌላዎች፡ጕዳይ፡እንደሚገ፟ባ፟፡ኾኖ፡መከራን፡አይቀበል፤
16፤ክርስቲያን፡እንደሚኾን፡ግን፡መከራን፡ቢቀበል፡ስለዚህ፡ስም፡እግዚአብሔርን፡ያመስግን፡እንጂ፡አይፈር።
17፤ፍርድ፡ከእግዚአብሔር፡ቤት፡ተነሥቶ፡የሚዠመርበት፡ጊዜ፡ደርሷልና፤አስቀድሞም፡በእኛ፡የሚዠመር፡
ከኾነ፡ለእግዚአብሔር፡ወንጌል፡የማይታዘዙ፡መጨረሻቸው፡ምን፡ይኾን፧
18፤ጻድቅም፡በጭንቅ፡የሚድን፡ከኾነ፡ዐመፀኛውና፡ኀጢአተኛው፡ወዴት፡ይታይ፡ዘንድ፡አለው፧
19፤ስለዚህ፥ደግሞ፡እንደእግዚአብሔር፡ፈቃድ፡መከራን፡የሚቀበሉ፥መልካምን፡እያደረጉ፡ነፍሳቸውን፡
ለታመነ፡ፈጣሪ፡ዐደራ፡ይስጡ።