ከ«ቅዱስ ጴጥሮስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ |
Tags: በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ |
||
መስመር፡ 9፦
፩ኛ ጴጥሮስ
ምዕራፍ ፩
መዠመሪያዪቱ፡የሐዋርያው፡
የጴጥሮስ፡መልእክት።
ምዕራፍ፡1፤
1-2፤የኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ሐዋርያ፡ጴጥሮስ፥እግዚአብሔር፡አብ፡አስቀድሞ፡እንዳወቃቸው፡በመንፈስም፡
እንደሚቀደሱ፥ይታዘዙና፡በኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ደም፡ይረጩ፡ዘንድ፡ለተመረጡት፡በጳንጦስና፡በገላትያ፡
በቀጰዶቅያም፡በእስያም፡በቢታንያም፡ለተበተኑ፡መጻተኛዎች፤ጸጋና፡ሰላም፡ይብዛላችኹ።
3-5፤ኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ከሙታን፡በመነሣቱ፡ለሕያው፡ተስፋና፡ለማይጠፋ፥እድፈትም፡
ለሌለበት፥ለማያልፍም፡ርስት፡እንደ፡ምሕረቱ፡ብዛት፡ኹለተኛ፡የወለደን፡የጌታችን፡የኢየሱስ፡ክርስቶስ፡
አምላክና፡አባት፡ይባረክ፤ይህም፡ርስት፡በመጨረሻው፡ዘመን፡ይገለጥ፡ዘንድ፡ለተዘጋጀ፡መዳን፡በእምነት፡
በእግዚአብሔር፡ኀይል፡ለተጠበቃችኹ፡ለእናንተ፡በሰማይ፡ቀርቶላችዃል።
6-7፤በዚህም፡እጅግ፡ደስ፡ይላችዃል፥ነገር፡ግን፥በእሳት፡ምንም፡ቢፈተን፡ከሚጠፋው፡ወርቅ፡ይልቅ፡
አብልጦ፡የሚከብር፡የተፈተነ፡እምነታችኹ፥ኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ሲገለጥ፥ለምስጋናና፡ለክብር፡ለውዳሴም፡ይገኝ፡
ዘንድ፡አኹን፡ለጥቂት፡ጊዜ፡ቢያስፈልግ፡በልዩ፡ልዩ፡ፈተና፡ዐዝናችዃል።
8-9፤ርሱንም፡ሳታዩት፡ትወዱታላችኹ፤አኹንም፡ምንም፡ባታዩት፡በርሱ፡አምናችኹ፥የእምነታችኹን፡ፍጻሜ፡
ርሱም፡የነፍሳችኹን፡መዳን፡እየተቀበላችኹ፥በማይነገርና፡ክብር፡በሞላበት፡ሐሤት፡ደስ፡ይላችዃል።
10፤ለእናንተም፡ስለሚሰጠው፡ጸጋ፡ትንቢት፡የተናገሩት፡ነቢያት፡ስለዚህ፡መዳን፡ተግተው፡እየፈለጉ፡መረመሩት፤
11፤በእነርሱም፡የነበረ፡የክርስቶስ፡መንፈስ፥ስለክርስቶስ፡መከራ፡ከርሱም፡በዃላ፡ስለሚመጣው፡ክብር፡
አስቀድሞ፡እየመሰከረ፥በምን፡ወይም፡እንዴት፡ባለ፡ዘመን፡እንዳመለከተ፡ይመረምሩ፡ነበር።
12፤ለእነርሱም፡ከሰማይ፡በተላከ፡በመንፈስ፡ቅዱስ፡ወንጌልን፡የሰበኩላችኹ፡ሰዎች፡አኹን፡ባወሩላችኹ፡ነገር፡
እናንተን፡እንጂ፡ራሳቸውን፡እንዳላገለገሉ፡ተገለጠላቸው፤ይህንም፡ነገር፡መላእክቱ፡ሊመለከቱ፡ይመኛሉ።
13፤ስለዚህ፥የልቡናችኹን፡ወገብ፡ታጥቃችኹና፡በመጠን፡ኖራችኹ፥ኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ሲገለጥ፡የምታገኙትን፡
ጸጋ፡ፈጽማችኹ፡ተስፋ፡አድርጉ።
14፤እንደሚታዘዙ፡ልጆች፡ባለማወቃችኹ፡አስቀድሞ፡የኖራችኹበትን፡ምኞት፡አትከተሉ።
15-16፤ዳሩ፡ግን፦እኔ፡ቅዱስ፡ነኝና፡ቅዱሳን፡ኹኑ፡ተብሎ፡ስለ፡ተጻፈ፡የጠራችኹ፡ቅዱስ፡እንደ፡ኾነ፡
እናንተ፡ደግሞ፡በኑሯችኹ፡ዅሉ፡ቅዱሳን፡ኹኑ።
17፤ለሰው፡ፊትም፡ሳያደላ፡በያንዳንዱ፡ላይ፡እንደ፡ሥራው፡የሚፈርደውን፡አባት፡ብላችኹ፡ብትጠሩ፡
በእንግድነታችኹ፡ዘመን፡በፍርሀት፡ኑሩ።
18-19፤ከአባቶቻችኹ፡ከወረሳችኹት፡ከከንቱ፡ኑሯችኹ፡በሚያልፍ፡ነገር፡በብር፡ወይም፡በወርቅ፡
ሳይኾን፥ነውርና፡እድፍ፡እንደ፡ሌለው፡እንደ፡በግ፡ደም፡በክቡር፡የክርስቶስ፡ደም፡እንደ፡ተዋጃችኹ፡
ታውቃላችኹ።
20-21፤ዓለም፡ሳይፈጠር፡እንኳ፡አስቀድሞ፡ታወቀ፥ነገር፡ግን፥እምነታችኹና፡ተስፋችኹ፡በእግዚአብሔር፡
ይኾን፡ዘንድ፥ከሙታን፡ባስነሣው፡ክብርንም፡በሰጠው፡በእግዚአብሔር፡በርሱ፡ስለምታምኑ፡ስለ፡እናንተ፡በዘመኑ፡መጨረሻ፡ተገለጠ።
22፤ለእውነት፡እየታዘዛችኹ፡ግብዝነት፡ለሌለበት፡ለወንድማማች፡መዋደድ፡ነፍሳችኹን፡አንጽታችኹ፡ርስ፡
በርሳችኹ፡ከልባችኹ፡አጥብቃችኹ፡ተዋደዱ።
23፤ዳግመኛ፡የተወለዳችኹት፡ከሚጠፋ፡ዘር፡አይደለም፥በሕያውና፡ለዘለዓለም፡በሚኖር፡በእግዚአብሔር፡
ቃል፡ከማይጠፋ፡ዘር፡ነው፡እንጂ።
24፤ሥጋ፡ዅሉ፡እንደ፡ሣር፡ክብሩም፡ዅሉ፡እንደ፡ሣር፡አበባ፡ነውና፤ሣሩ፡ይጠወልጋል፡አበባውም፡
ይረግፋል፤
25፤የጌታ፡ቃል፡ግን፡ለዘለዓለም፡ይኖራል።በወንጌልም፡የተሰበከላችኹ፡ቃል፡ይህ፡ነው።
==ምዕራፍ ፪==
|