ከ«መልከ ጼዴቅ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 23፦
ከዚህ በላይ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ስለ መልከ ጼዴቅ የተለያዩ ትምህርቶችና ታሪኮች አሉ።
 
===ብቅሌምንጦስ ሥነ ጽሑፍ===
*''[[ኪታብ አል-ማጋል]]'' በ[[ቅሌምንጦስ ሥነ ጽሑፍ]] ውስጥ ይመደባል። በዚህ ጹሑፍ ዘንድ፣ [[ሰብአ ሠገል]] ብራናውን ለክርስቶስ በሕጻንነቱ እንደ ስጦታ ሰጡት፣ እሱም ለ[[ጴጥሮስ]]፣ ጴጥሮስም በኋላ የሮሜ [[ፓፓ]] ለሆነው ለ[[ቅሌምንጦስ]] ያቀረበው ታሪክ ነው። በዚህ መሠረት፣ የመልከ ጼዴቅ አባት የ[[አርፋክስድ]] ልጅ ማሊኽ እንደ ነበር እናቱም ዮጻዳቅ እንደ ተባለች የአርፋክስድ አባት ሴም በጻፈው መዝገብ እንደ ተገኘ ይጨምራል። ከዚህ በላይ፣ በ[[ኖህ]] ትዕዛዝ ሴምና መልከ ጼዴቅ አብረው ወደ [[አራራት]] ሔደው የ[[አዳም]]ን ሬሳ ከ[[ኖህ መርከብ]] አወጡት። ከዚያ በሗላ፣ በመላዕክት ዕርዳታ ወደ ኢየሩስሌም ዞረው በ[[ጎልጎታ]] ኮረብታ ውስጥ አቀበሩት። አብራም በእግዚአብሔር ትዕዛዝ [[ይስሐቅ]]ን እንደ መሥዋዕት ወደ መሥዊያ ቦታ ባመጣው ጊዜ፣ የነበሩበት ኮረብታ ጎልጎታ ሲሆን የመልከ ጼዴቅ መሥዊያ ቦታ ነበር። ያንጊዜ የአሕዛብ ነገሥታት ስለ መልከ ጼዴቅ ዝና ሰምተው ለበረከት ወደርሱ መጥተው ነበር። እነዚህ ነገሥታት ሁሉ ወዲያው ከተማ ለመልከ ጼዴቅ ሠሩለት፣ ስሙን «እየሩሳሌም» አለው። ነጉሦቹም እንደሚከተሉ ይዘርዝራሉ፦ የ[[ጌራራ]] ንጉሥ [[አቢሜሌክ]]፣ የ[[ሰናዖር]] ንጉሥ [[አምራፌል]]፣ የዴላሳር ([[ኤላሳር]]) ንጉሥ [[አርዮክ]]፣ የ[[ኤላም]] ንጉሥ ኮሎዶጎምር፣ የሕዝብ ንጉሥ ቲዳል ([[ቲርጋል]])፣ የሰዶም ንጉሥ ቤራ (ባላ)፣ የ[[ገሞራ]] ንጉሥ ብርሳ፣ የ[[አሞራውያን]] ንጉሥ ስምዖን፣ የ[[ሳባ]] ንጉሥ ሲማይር፣ የቤላ ([[ዞዓር]]) ንጉሥ ቢስላህ፣ የ[[ደማስቆ]] ንጉሥ ህያር፣ እና የበረሃዎች ንጉሥ ያፍታር ናቸው። ከዚህም በኋላ የ[[ቴማን]] ንጉሥ ማዋሎን የመልከ ጼዴቅን በረከት ለማግኘት ወደ እየሩሳሌም ተጓዘ ይላል።<ref>[http://www.sacred-texts.com/chr/aa/aa2.htm ኪታብ አል-ማጋል] {{en}}</ref>
 
Line 29 ⟶ 30:
እነዚህ ምንጮች እንደሚሉን፣ ከአራራት ወደ ጎልጎታ ተመልሰው ሴም መልከ ጼዴቅን ለምንኩስና በምስጢር ሾመው። ወላጆቹ ማላሕና ዮጻዳቅ «ልጃችን ወዴት ነው?» ጠይቀው ሴም «በመንገድ ላይ ዐረፈ» ሲላቸው ዕውነት መስሎአቸው አለቀሱለት። መልከ ጼዴቅ ከሴም ሹመት በኋላ ቆዳ ለባሽ፣ ከጎልጎታ አቅራቢያ መቸም የማይራቅ፣ እንደ [[ናዝራዊ]] ጽጉሩን መቸም ያላቋረጠ ካህን ሆነ። አብራምን መጀመርያ ባገናኘው ጊዜ ግን መልከ ጼዴቅ በእግዜር ትዕዛዝ የራሱን ጥፍሮች አቋረጠ። 12 ንጉሦቹ በጽድቁና በመልካምነቱ አድንቀው ወደ አገሮቻቸው እንዲመጣ ቢለምኑት ከዚህ መራቅ አልችልም ብሎ እምቢ አላቸው። ስለዚህ በሠፈሩ እየሩሳሌምን የሠሩለት ነው። በኋላም የይስሐቅ ሚስት [[ርብቃ]] ርጉዝ በሆነችበት ሰዓት ሁለት አገራት (ማለት [[ኤዶምያስ]]ና [[እስራኤል]]) በማሕፀንሽ አሉ ብሎ የነበየላት መልከ ጼዴቅ እንደ ነበር በነዚህ መጻሕፍት ይነገራል።
 
===በመጽሐፈ ሄኖክ ካልእ===
''[[መጽሐፈ ሄኖክ ካልእ]]'' ወይም ''ስላቮኒክ ሄኖክ'' የታወቀው ከ[[ጥንታዊ ስላቮንኛ]] ቅጂዎች ሲሆን በአንዳንድ ቅጂ ስለ መልከ ጼዴቅ በፍጹም የሚለዩ ልማዶች ያቀርባል። ብዚህ መሠረት ከማየ አይኅ አስቀድሞ የ[[ኖኅ]] ወንድም ኒር ሚስጥ ሶፓኒም መካን ስትሆን በእርጅናዋ በድንግልናዋ በተዓምር መልከ ጼዴቅን እየወለደች ሞተች። ልጁም ዐዋቂ ሆኖ ተወለደ። ከዚያ መልአኩ [[ገብርኤል]] ወደ [[ኤድን ገነት]] ወሰደው፤ ስለዚህ መልከ ጼዴቅ በኖኅ መርከብ ላይ ሳይሆን ከጥፋት ውኃ ማምለጥ ቻለ ይላል። ይህ ታሪክ ምናልባት በዕብራይስጥ በ 60 አም እንደ ተቀነባበረ ይታስባል።
 
===በቁምራንና በናግ ሐማዲ ብራናዎች===
በ[[ሞት ባሕር]] ወይም [[ቁምራን ጥቅል ብራናዎች]] መካከል አንዱ «[[የመልከ ጼዴቅ ሰነድ]]» ወይም 11Q13፣ እንዲሁም በ[[ኖስቲሲሲም]] እምነት ጽሑፎች በ[[ናግ ሐማዲ]] ግብጽ መካከል አንዱ፣ መልከ ጼዴቅ በ[[ፍርድ ቀን]] የሚመጣ የአምላክ መሲሕ መጠሪያ (ጽድቅ ንጉሥ) ነው።
 
 
===በአይሁድ ትጸ
<references/>