ከ«አካድኛ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''አካድኛ''' ወይም '''አሦርኛ''' ወይም '''ባቢሎንኛ''' በጥንት በ[[መስጴጦምያ]] የተናገረ [[ሴማዊ ቋንቋ]] ነበረ።
 
በሥነ ቅርስ መጀመርያው የታወቀው አካድኛ ጽሑፍ ከ[[መስኪአጝ-ኑና]] ዘመን (2314 ዓክልበ. ግድም) ነው። ከ[[አካድ]] ንጉሥ [[ታላቅ ሳርጎን]] ጀምሮ የአካድ መንግሥት (2077-2010 ዓክልበ.) በመላው መስጴጦምያ፣ [[ኤላም]]ና [[ሶርያ]] አስገደዱት። ከዚያ በኋላ ኤላም ወደ [[ኤላምኛ]] መለሰ፣ የሶርያም ቋንቋ [[ኤብላኛ]] ሆነ። በ[[አሦር]]ና በ[[ባቢሎን]] የአካድኛ አይነቶች ተነገሩ። አሦራውያን በ[[አናቶሊያ]] ([[ሐቲ]]) የ[[ካሩም]] ንግድ እስከ 1628 ዓክልበ. ድርስ ያሕል ያካሄዱ ነበር፤ የአሦርኛ አካድኛ ጥቅም እንደ መደበኛ ወይም ይፋዊ ጽሑፍ ቋንቋ አስፋፉ።
 
በሚከተለው ዘመን በ[[ግብጽ]] የተገኙ [[የአማርና ደብዳቤዎች]] (1369-1339 ዓክልበ.) እንዳሳዩ፣ ጽሕፈት የነበራቸው አገራት ሁሉ አካድኛ እንደ መደበኛ ቋንቋ ይጠቀሙ ነበር። የ[[ጥንታዊ ግብጽ]]፣ የ[[ከነዓን (ጥንታዊ አገር)|ከነዓን]]፣ የ[[ሚታኒ]]፣ የ[[ኬጥያውያን መንግሥት]]፣ የ[[ባቢሎን]] (ካራንዱኒያሽ)፣ የ[[አላሺያ]] ወይም የ[[አርዛዋ]] ባለሥልጣናት ሁላቸው በአካድኛ ተነጋገሩ። እነዚህ አገራት ግን ለየራሳቸው ልሳናት [[ግብጽኛ]]፣ [[ከነዓንኛ]]፣ [[ሑርኛ]]፣ [[ኬጥኛ]]፣ [[ካሥኛ]]፣ [[ሚኖአንኛ]] እና [[ሉዊኛ]] ነበሩዋቸው።
 
በ740 ዓክልበ. የአሦር ንጉሥ [[3 ቴልጌልቴልፌልሶር]] [[አረማይስጥ]] ከአሦርኛ ጋር ይፋዊና መደበኛ ቋንቋ አደረገው። ከዚያ ጀምሮ የአረማይስጥ ጥቅም እየተስፋፋ የአካድኛ ጥቅም በየጊዜ ይቀነስ ነበር። ከአዲስ ባቢሎን መንግሥት ውድቀት በኋላ አካድኛ ባይነገርም አካድኛን መጻፍ የቻሉ ጥቂት ሊቃውንት ምናልባት እስከ 100 ዓም ያህል ቀሩ።
 
== ደግሞ ይዩ ==