ከ«ዝግመተ ለውጥ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 8፦
[[ባለሙያ ንድፍ]] የተባለው ትምህርት ከሥነ በራሂ ጥናት የምንማረው መረጃ ሁሉ በፈጣሪው እቅድ እንደ ሆነ ለመግለጽ ይሞክራል። በተለይ በ[[መጽሐፍ ቅዱስ]] ምዕራፍ ፩፡፳፮ መሠረት በመሰለ ስሜት፣ «ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፣ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፣ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፣ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ» ይላል።
 
የሰው ልጅ [[ሐብለ በራሂ]] (ክሮሞሶም) ከሕያዋን ሁሉ በተለይ ለ[[ቺምፓንዚ]] [[ጦጣ]] ሐብለ በራሂ ዝምድና እንዳለው ተገልጿል። ቺምፓንዚ ግን እንደ ሰው ልጅ ሳይሆን ሌሎችን እንስሳት ወይም አትክልት ለማዳ ለማድረግ እንዳልተዘጋጀ ግልጽ ነው። በዝርዝሩ ስንመልክተው፣ የሰው ልጅ ሐብለ በራሂና የቺምፓንዚ ሐብለ በራሂ የሚለያዩ በአንዱ እሱም በሰዎች [[፪ኛው ሐብለ በራሂ]] ሲሆን፣ በቺምፓንዚ ግን በዚያው ሥፍራ ሁለት ልዩ ልዩ አጫጭር ሐብለ በራሂዎች አሉዋቸው። ከዚህ መረጃ የቺምፓንዚ ሐብለ በራሂ ወደ ሰው ልጅ ሐብለ በራሂ ለመቀይር፣ እነዚህ ሁለት ልዩ ልዩ አጫጭር ሐብለ በራሂዎች አንድላይ በትክክል በፍጹምነት በጥንቃቄ በእቅድ ማጋጥምና ማዋኸድ አስፈለገ። ይህ ድርጊት ተዓምር መሆን ነበረበትና ለ«ባለምያ ንድፍ» እንደ ማስረጃ ይቆጠራል። ስለዚህ የሰው ልጅ ክሮሞሶም በአንድ ትውልድ መከሠት ነበረበት እንጂ በብዙ ሚሊዮን ዘመን ዝግታዊ ሂደት የሚለወጥ አይመስልም። በተጨማሪ፣ ድርጊቱ ወይም በጦጣ ማሕጸን ወይም በምድሪት ምስጢራዊ ገበታ ላይ እንደ ተፈጸመ ማወቅ አንችልም ይላል፤ የሰው ልጅ በራሂ አራያ ከቺምፓንዚ በራሂ አራያ የተለወጠበትም ዘመን ከ6000 ዓመታት በፊት አይሆንም ይላል።
 
{{መዋቅር}}