ከ«ሰይጣን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
+
መስመር፡ 5፦
ሰይጣን ሌላው ስሙ [[ዲያብሎስ]] ነው። ሰይጣን ከመሰይጠኑ በፊት የነበረው ስም ሳጥናኤል ሲሆን በዕብራይስጥ አዛዝኤል ይባላል። "አዛዝ" ማለት "ጥንካሬ" ማለት ሲሆን "ኤል" ማለት አምላክ ማለት ነው፤ "አምላክ ጥንካርዬ ነው" ማለት ነው።
 
በ[[ዕብራይስጥ]] የ«ሰይጣን» ትርጉም «ተቃዋሚ» ሲሆን የ[[እግዚአብሔር]]ን ዕቅዶች የሚቃወም ማናቸውም መንፈስ ሊሆን ይችላል። ስለዚህ በ[[ማቴዎስ ወንጌል]] 16:23 እና [[ማርቆስ ወንጌል]] 8:33 [[ጴጥሮስ]] ለ[[ኢየሱስ]] ይህ ያልከው ስቅለትህ አይሁን! ሲለው ኢየሱስ ጴጥሮስንም «ሰይጣን» ይለዋል። አዛዜል የተባለው ከ[[ሴት (የአዳም ልጅ)]] ተወላጆች መካከል ያመጸ ሰው እንደ ነበር በአንዳንድ ልማዶች ይታመናል። ያው ሰይጣን በ[[መጽሐፈ ሄኖክ]] ዘንድ ፍዳውን አገኝቶታል። ከአዛዜልም በፊት በ[[እባብ]] ወይም ከአዛዜልም በኋላ ወደፊት ማናቸውም ተቃዋሚ መንፈስ ወይም ሠይጣን እንዲሁም ፍዳውን ያገኛል። በማርቆስ 3:25-26 ኢየሱስ ስለ ሠይጣን እንዳስተማረ «እርስ በርስ የተለያየ ቤት» ሲለው፣ ሰይጣን በራሱ ላይ ተለያቶ እንደ ሆነ እንጂ ክፉው በአንድ በተዋኸደ ፈቃድ እንደማይመራ ያሳያል።
 
በአብርሃማዊ ትምህርቶች ዘንድ ሰው ሁሉ ወይም በ[[ኅሊና]] ወይም በ[[ትዕቢት]] እንደየመጠኑ እንዲመራ [[ነጻ ፈቃድ]] የተሰጠ ሲሆን፣ በአንዳንድ ሰዎች እምነቶች ግን አምላኩና ሠይጣኑ በእኩልነት ሃይለኛ ይሆናሉ የሚለው ሀሣብ መጀመርያ በ[[ዞራስተር]] ትምህርቶች እንደ ተገኘ ይባላል።