ከ«ሰይጣን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
ተጨማሪ
ተጨማሪ
መስመር፡ 6፦
 
በ[[ዕብራይስጥ]] የ«ሰይጣን» ትርጉም «ተቃዋሚ» ሲሆን የ[[እግዚአብሔር]]ን ዕቅዶች የሚቃወም ማናቸውም መንፈስ ሊሆን ይችላል። ስለዚህ በ[[ማቴዎስ ወንጌል]] 16:23 እና [[ማርቆስ ወንጌል]] 8:33 [[ጴጥሮስ]] ለ[[ኢየሱስ]] ይህ ያልከው ስቅለትህ አይሁን! ሲለው ኢየሱስ ጴጥሮስንም «ሰይጣን» ይለዋል። አዛዜል የተባለው ከ[[ሴት (የአዳም ልጅ)]] ተወላጆች መካከል ያመጸ ሰው እንደ ነበር በአንዳንድ ልማዶች ይታመናል። ያው ሰይጣን በ[[መጽሐፈ ሄኖክ]] ዘንድ ፍዳውን አገኝቶታል። ከአዛዜልም በፊት በ[[እባብ]] ወይም ከአዛዜልም በኋላ ወደፊት ማናቸውም ተቃዋሚ መንፈስ ወይም ሠይጣን እንዲሁም ፍዳውን ያገኛል።
 
በአብርሃማዊ ትምህርቶች ዘንድ ሰው ሁሉ ወይም በ[[ኅሊና]] ወይም በ[[ትዕቢት]] እንዲመራ [[ነጻ ፈቃድ]] የተሰጠ ሲሆን፣ በአንዳንድ ሰዎች እምነቶች ግን አምላኩና ሠይጣኑ በእኩልነት ሃይለኛ ይሆናሉ የሚለው ሀሣብ መጀመርያ በ[[ዞራስተር]] ትምህርቶች እንደ ተገኘ ይባላል።
 
በአብርሃማዊ ትምህርቶች ደግሞ አምላኩ እንደ ብርሃን ሲሆን፣ ሰይጣን ግን ጉድጓዶች የማይታይበት ጥላውን ወይም ሌሊት እንደሚመርጥ ይባላል። በ[[አረመኔ]] [[ግሪክ አገር]] ወይም [[ሮሜ መንግሥት]] ባሕል ግን፣ ይህን ገልብጠው ክፉው ብርሃኑን የሚያመጣ ይሆናል ስላሉ፣ የ[[ሮማይስጥ]] ስያሜ «ሉሲፈር» («ብርሃን አምጪ») ተቀበለ። ይህ ርዕዮተ አለም በመጽሐፍ ቅዱስ ባይደገፍም፣ የሮማይስጥ ትርጉምና ብዙ የአውሮጳ ትርጉሞች በ[[ትንቢተ ኢሳይያስ]] 14:12 በ«የአጥቢያ ኮከብ» ፈንታ «ሉሲፈር» የሚለውን ስያሜ አስገብተዋል። ንባቡ በኦሪጂናሉ ዕብራይስጥ በሙሉ ሲነበብ ግን «የአጥቢያ ኮከብ» የተባለው የ[[ባቢሎን]] ንጉሥ [[፪ ናቡከደነጾር]] እንደ ሆነ ግልጽ ነው። ስለዚህ ከዚሁ ጥቅስ ሰይጣናዊ መረጃ ደርሷል የሚለው ትምህርት ውሸት ነው።
 
{{መዋቅር-ሃይማኖት}}