ከ«ምክር ቤታዊ አገባብ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 3፦
በዝርዝሩ ደንቦቹ እንደየድርጅቱ ሊለዩ ይችላሉ። መንግስት ላልሆኑ ድርጅቶች፣ በዋነኝነት የሚከተለው ''[[የሮበርት ቅደም-ተከተል ደንቦች]]'' የተባለው መምሪያ መጽሐፍ ነው። የ[[አሜሪካ]] ብሔራዊ ምክር ቤቶች ''[[የጄፈርሶን ፓርላሜንታዊ መምሪያ]]'' ይከተላሉ። የ[[ዩናይትድ ኪንግደም]] ፓርላማ ''[[የእርስክን መይ ፓላሜንታዊ ሂደት መምሪያ]]'' ይከተላል። ከአሜሪካ 99 ክፍላገራዊ ምክር ቤቶች<ref>[[ነብራስካ]] አንድ ምክር ቤት አለው፣ ሌሎቹ 49 ክፍላገራት ሁለት፣ = 99። </ref>፣ 70 ''[[የመይሶን ምክር ቤታዊ አገባብ መምሪያ]]'' ሲከተሉ፣ 13 በ''ጄፈርሶን መምሪያ''፣ 4 በ''ሮበርት መምሪያ'' ይገዛሉ። ከነዚህ ዋናዎቹ ፓርላሜንታዊ መምሪያዎች ሌሎች አሉ። ብዙ ጊዜ ድርጅቶች ከነዚህ መሠረቶች ለራሳቸው የቅደም-ተከተል ሂደት ደንቦች ለማስተካከል በምርጫ ይስማማሉ።
 
በፓርላሜንታዊ ሂደት አንድ ማዕከለኛ መርህ «ውሳኔ በድምጽ ብዛት ይወሰናል» የሚል ነው። ከስብሰባው አካላት ወይም «መቀመጫዎች» መካከል፣ አንዱ አባል በተራው («ወለል»ን ሲይዝ) ሃሣቡን ለ«ሊቀ ወምበር» ማቅረብ ይችላል። ሀሣቡ በተለይ ለቁርጥ ሀሣብ እንዲሆን ከሆነ፣ በጽሑፍም ይቀርባል። በልማድ፣ ለሀሣቡ በቂ ትኩረት እንዳለ ለማሳየት፣ ሁለተኛ አባል «ሃሣቡን እደግማለሁ» ማለት አለበት። ከዚያ በቅደም-ተከተሉ ሲነሣ የተገኙት አባላቱ ሁሉ በተራቸው ስለ ሀሣቡ አስተያየት፣ ምክርና ክርክር ውይይት ያደርጋሉ። የሀሣቡን ረቂቅ ጽሑፍ ቃላት ለመቀይር በንዑስ-ሀሣብ የሚፈልጉ ሊኖሩ ይቻላል። አባላቱ በዋና ሀሣብ ሳይወስኑ መጀመርያ ስለዚያው ንዑስ-ሀሣብ ወይም ቃላት ለውጥ መወሰን አለባቸው።
 
ምርጫው በድምጽ ብዛት ሲባል፣ ይህ ለቀላል ጥያቄ በውነት በድምጽ ብዛት «አዎ» ወይም «አይ» በመጮህ ሊደረግ ይችላል። ስምምነት መኖሩ ካልመሰለ፣ እያንዳንዱ አባል በየተራው «አዎ» ወይም «አይ» በመጮህ፣ በጽሑፍ ምርጫ፣ በምስጢራዊ (የአምራጮች መታወቂያ በማይገለጽበት) ቆጠራ ወይም በልዩ ልዩ ዘዴዎች ሊቆጠር ይቻላል።