ከ«የአስተሳሰብ ሕግጋት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
 
መስመር፡ 1፦
'''የአስተሳሰብ ሕግጋት''' ማለት ማናቸውም ስሜት የሚሰጡ ሐሳቦች ሊከተሉዋቸው የሚገቡ ሕግጋት ማለት ነው። ይህ ፈላስፎች በዘመናት ላይ ያገኙት አንድ የ[[ሥልጣኔ]] ምርት ነው። እነዚህ ሕግጋት እጅግ መሠረታዊ እና ሁሉም የዕውቀት ዘርፍ ሊከተሏቸው የሚገባ ብቻ ሳይሆን በዕለት ተዕለት ኑሮ ሳይቀር ሊተገበሩ የሚገቡ ናቸው። የሕግጋቱ ብዛት ሦስት ሲሆን እንደሚከተለው ይዘረዘራሉ፦
 
:ሕግ '''፩)የተቃርኖ ሕግ'''፦ ሁለት [[ተቃራኒ]] [[ረቂቆች|ዓረፍተ ነገሮች]]፣ በአንድ ጊዜ እውነት ሊሆኑ አይችሉም። ወይንም በሌላ አነጋገር አንድ ዓረፍተ ነገር በአንድ ጊዜ እውነት እና ውሸት ሊሆን ከቶ አይችልም።
 
:ሕግ '''፪)መሃከል አግላይ ሕግ'''፦ አንድ [[ረቂቅ|ዓረፍተ ነገር]] ቢሰጥ፣ ወይ እራሱ እውነት ነው፣ ወይም ደግሞ ተቃራኒው እውነት ነው። ከዚህ ውጭ የሆነ፣ በሁለቱ ዓረፍተነገሮች መካከል ገብቶ እውነት የሆነ ሦስተኛ አረፍተ ነገር ፈጽሞ የለም። በሌላ አነጋገር፣ አንድ ዓረፍተ ነገር ወይም እውነት ነው ወይም ውሸት ነው እንጅ ሌላ ሦስተኛ ነገር ሊሆን አይችልም።
 
:ሕግ '''፫)የማንነት ሕግ'''፦ ሁሉም ነገር ከራሱ ጋር አንድ አይነት ነው። በሌላ አነገጋገር አንድ አረፍተ ነገር እውነት ከሆነ፣ እውነት ነው። ይሄ ሕግ በጣም ግልጽ ቢመስልም አንድ አንድ ጊዜ ጥርጣሬ ላይ ሊዎድቅ ይችላል። ለምሳሌ ''የመታገስ ቁመት ሜትር ከሃያ ነው።'' የሚለው ዓረፍተ ነገር የዛሬ አስር አመት እውነት ቢሆን፣ ዛሬ ቁመቱ ሲጨምር ውሸት ይሆናል። ይሁንና፣ ህጉ ለሚቀየሩ ነገሮች ሳይሆን ባሉበት ለረጉ ነገሮች ብቻ ነው የተደነገገው።