ከ«ፐሪብሰን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 7፦
ሴት ፐሪብሰን በተለይ ከቀድሞ ፈርዖኖች የሚለይበት ነገር አርእስቱ በኸንቲ-አመንቲው እና በሔሩ ስሞች የጀመረው ሳይሆን፣ በሐሩ ጠላት በሌላው ጣኦት [[ሴት (ግብጽ)|ሴት]] ስም ጀመረ። አንዳንዴም የ[[ሬ]] (የ[[ፀሐይ]] ጣኦት) ምልክት ከዚህ ጋር ይታያል። ፈርዖኖች በፊት ከሔሩ ወገን እየሆኑ፣ በሴት ወገን ላይ ጦር ዘመቻዎች ያድርጉ ነበር። አሁን ግን የሴት ወገን የወከለው ፈርዖን፣ ሴት ፔሪብሰን፣ ግብጽን እንደ ገዛ ይመስላል።
 
የፐሪብሰን ኅልውና ከመቃብሩና ከበርካታ ሥነ ቅርሶች ይታወቃል፤ አንዳንድ ጽሑፍ «ኢኒ-ሰትጨት» «የ[[ሰትጨት]] ሰዎች ግብር» ሲል ሰትጨት በኋላ ዘመን [[ከነዓን (ጥንታዊ አገር)|ከነዓን]] የተባለው ምድር እንደ ነበር ይታስባል። ፐሪብሰን በግብጽ ከሠሩት ከተሞች መሃል አንዱ «የሰትጨት (ሰዎች) ከተማ» ተባለ፤ ይህ ለሴት (ሰት) ወገን አንድ መጠሪያ እንደ ነበር ይቻላል።
 
በተጨማሪ ሌላ የንጉሥ ስም ሔሩ ስኸሚብ ወይም ሔሩ [[ሰኸሚብ-ፐረንመዓት]] በሥነ ቅርስ ተገኝቷል፤ በተለይ ይህ ስም በፐሪብሰን መቃብር ውስጥ ተገኝቷል። ለፈርዖን ሰኸሚብ እራሱ ግን መቃብር አይታወቅም፤ ብዙ ሊቃውንት ሁለቱ አንድ እንደ ነበሩ የሚል መላምት አላቸው። በዚህ አስተሳሰብ ፈርዖን ሔሩ-ሰኸሚብ-ፐረንመዓት ስያሜውን ቀይሮ ለዘመኑ መጨረሻ ፈርዖን ሴት-ፐሪብሰን ሆነ። እንዲህ ከሆነ ምናልባት ፈርዖኑ ታማኝነቱን ደግሞ ከሔሩ ወደ ሴት ወገን ቀየረው። ሌሎች ሊቃውንት ግን ሁለቱ የተለያዩ ነገሥታት እንደ ነበሩ ያምናሉ።